ከሰኔ ሀያ ስድስት ጀምሮ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት የሚካሄደው የዘንድሮው የውድድር ዓመት ሴካፋ ከ 23 ዓመታ በታች ተጫዋቾች ብቻ እንደሚሳተፉበት ይታወቃል ።
ከ ሰኔ 26 እስከ ሰኔ ሐምሌ 11 በኢትዮጵያ አዘጋጅነት በ ባህርዳር ከተማ በሚካሄደው በዚህ ውድድር ዲሞክራቲክ ኮንጎ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት ማሳየቷ ይፋ ሆኗል ።
ይህንንም ተከትሎ ዲሞክራቲክ ኮንጎ በሴካፋው አስራ ሁለተኛ ሀገር በመሆን ውድድሩን የተቀላቀለች ሀገር ሆናለች ።
በዘንድሮው የውድድር ዓመት ሴካፋ ላይ የሚሳተፉ ሀገራት 20,000 የአሜሪካ ዶላር ለውድድሩ ማስኬጃ ከምድብ ድልድሉ አስቀድሞ መክፈል ይጠበቅባቸዋል ።
ከ ዲሞክራቲክ ኮንግ በተጨማሪ ሀገራችንን ኢትዮጵያ ጨምሮ ዩጋንዳ ፣ ኤርትራ ፣ ጅቡቲ ፣ ሱዳን ፣ ደቡብ ሱዳን ፣ ኬንያ ፣ ታንዛኒያ ፣ ዛንዚባር ፣ ቡሩንዲ ፣ ሩዋንዳ እና ሶማሊያ የሚሳተፉ ሀገራት ናቸው ።
አስተያየት ይስጡ