ሰበር ዜና ……
የኢትዮጵያ እግርኮስ ፌዴሬሽን የዲሲፕሊን ኮሚቴ አርቢትር ዶክተር ሃይለየሱስ ባዘዘው ላይ የዳኞች ኮሚቴ ያቀረበውን ክስ ውድቅ አደረገ።
ባለፉት አራት ወራት በክስ ሂደት ሲታይ የቆየው አርቢትሩ ከቀረበበት ከእውነት የራቀ ክስ ነጻ ነህ ብሎታል
ዛሬ ይፋ በሆነ መረጃ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ዳኞች ኮሚቴ ያቀረበው ክስ ተቀባይነት የሌለውና በማስረጃ ያልተደገፈ መሆኑን በመግለጽ የባለሙያዎች ህገመንግስታዊ ሃሳብን የመግለጽ መብትን ማክበር እንዳለባቸው አሳስቧል። የብሄራዊ ዳኞች ኮሚቴ ከሳሽም ሆነ ምስክር መሀን እንደማይችልም በመግለጽ ዶክተር ሃይለየሱስን ነጻ በማድረግ ዘግይቶሞ ቢሆን የፍትህ ምላሽ ሰጥቷል።
የዲሲፕሊን ኮሚቴ ውሳኔን ተከትሎ አርቢትሩን ጨዋታ ላይ የመመደብ መብቱ እንዲከበር ጽ/ቤቱ መመሪያ እንደሚሰጥ ይጠበቃል። ባለፉት አራት ወራት ከምደባ የታገደው ዶክተር ሃይለየሱስ ከካፍ የጨዋታ ምደባ እንዲታገድ በዲፓርትመንቱ የተሰራው አላሴፈላጊ ተግባር ዳግም በሀገር ወስጥ ውድድር ላይ
እንዳይፈጸም የጽ/ቤቱ ክትትል ወሳኝነት እንዳለው ይታመናል።


