የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
1. አሳምነው ገብረወልድ (ኢትዮ ኤሌትሪክ ) /ረዳት አሰልጣኝ : ክለባቸው ከ ሃዋሳ ከተማ ጋር ባደረገው የ18ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 89 ኛ ደቂቃ ላይ ዳኛን አፀያፊ ስድብ በመሳድብ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገዱ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦባቸዋል ።
ስለሆነም የቡድን አመራሩ ለፈፀሙት ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 66 በተቁ 1 መሰረት 6 ጨዋታ እንዲታገዱ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍሉ የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
2. ዮናስ ለገስ(ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) : ክለቡ ከ ነገሌ አርሲ ጋር ባደረገው የ18ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 48ኛ ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ።
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.አ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የየውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
3. ኤፍሬም ታምራት (አርባምንጭ ከተማ) : ከታች በተጠቀሱት ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- አርባምንጭ ከተማ-ሸገር ከተማ
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አርባምንጭ ከተማ
- አርባምንጭ ከተማ ፋሲል ከነማ
- ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ-አርባምንጭ ከተማ
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.አ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
- ማሰታውቂያ -
4. ቢኒያም ካሣሁን (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) : ከታች በተጠቀሱት ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድተመልክቷል ።
- መቐለ 70 እንደርታ-ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ-ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ-ሀዲያ ሆሳዕና
- ኢትዮ ኤሌትሪክ -ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነገሌ አርሲ
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.አ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
5. ወንድማገኝ ማዕረግ (ሃዋሳ ከተማ) : ከታች በተጠቀሱት ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድተመልክቷል ።
- ሲዳማ ቡና-ሃዋሳ ከተማ
- ሃዋሳ ከተማ-ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
- ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ-ሃዋሳ ከተማ
- ሃዋሳ ከተማ-መቻል
- ሃዋሳ ከተማ-ኢትዮ ኤሌትሪክ
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.አ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል ውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
6. በረከት ሳሙኤል (ሃዋሳ ከተማ) : ከታች በተጠቀሱት ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ሲዳማ ቡና-ሃዋሳ ከተማ
- ሸገር ከተማ-ሃዋሳ ከተማ
- ሃዋሳ ከተማ-ሀዲያ ሆሳዕና
- አርባምንጭ ከተማ-ሃዋሳ ከተማ
- ሃዋሳ ከተማ-ኢትዮ ኤሌትሪክ
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.አ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅካት ብር 1500 እንዲከፍል ውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
7. አሚኑ ነስሩ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) : ከታች በተጠቀሱት ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ባህርዳር ከተማ-ቅዱስ ጊዮርጊስ
- ቅዱስ ጊዮርጊስ-ኢትዮጵያ መድን
- ቅዱስ ጊዮርጊስ-ሀዲያ ሆሳዕና
- ቅዱስ ጊዮርጊስ-ምድረ ገነት ሽረ
- ፋሲል ከነማ-ቅዱስ ጊዮርጊስ
ስለሆነም ተጨዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.አ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
8. ከቤ ቡዙነህ (ነገሌ አርሲ): ከታች በተጠቀሱት ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድተመልክቷል
- ነገሌ አርሲ-ሸገር ከተማ
- ምድረ ገነት ሽረ -ነገ አርሲ
- ሃዋሳ ከተማ-ነገሌ አርሲ
- ነገሌ አርሲ-ሲዳማ ቡና
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ-ነገሌ አርሲ
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.አ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
9. ሃዋሳ ከተማ ክለቡ ከኢትዮ ኤሌትሪክ ጋር ባደረገው የ18 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የሃዋሳ ከተማ ቡድን ተጫዋች የሆኑት
- በረከት ሳሙኤል
- ወንድማገኝ ማዕረግ
- ጌታነህ ከበደ
- ዝያድ ከድር
- እስራኤል እሸቱ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 65 (ሀ) መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 / አምስት ሺ/ እንዲከፍል ውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
የተሰተካካይ ጨዋታ መርሀ ግብር
ከበዓል ጋር በተያያዘ ምክኒያት ለሌላ ጊዜ ተላልፎ የነበረው የፋሲል ከነማ ና ሀዲያ ሆሳዕና ጨዋታ ሰኞ የካቲት 2 2018 ከሰዓት በ9:0ዐ በአዲስ አበባ ስታድየም እንዲደረግ የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።


