መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ 22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ 22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ እሁድ ግንቦት 1 2013 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የተደረጉ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ግጥሚያ(ዎች) ከዳኞች እና ከታዛቢዎች የቀረቡለትን የዲሲፕሊን ሪፖርት ከመረመረ በኋላ የተለያዩ ውሳኔዎችን አስተላልፏል ።

1. ላሚን ኩማረ (አዳማ ከተማ) ከ ድሬደዋ ከተማ ጋር ባደረገው የ 22 ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ ላይ በ79 ኛ ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ ቀይ ካርድ አይቶ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ።

ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ ወስኗል።

2. አዳማ ከተማ ክለቡ ከ ድሬደዋ ከተማ ጋር ባደረገው የ 22 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የ አዳማ ከተማ ቡድን ተጫዋች የሆኑት አሊሲ ኦቢሳ ጆናታን ፣ ላሚን ኩማረ ፣አሚኑ ነስሩ ፣ ላሚን ኩማረ ፣ ሳኮባ ካማራ በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺህ/ እንዲከፍል ወስኗል፡፡

3. ከድር ኩሊባሊ(ፋሲል ከነማ) በአምስት ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል።

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ እና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል ወስኗል።

4. በረከት ወልዴ(ወላይታ ድቻ) በተመሳሳይ አምስት ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል።

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ እና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል ወስኗል።

ጥሪ

ለሃዲያ ሆሳዕና ክለብ ስራ አስኪያጅ ፣ ለ ባህር ዳር ከተማ የቡድን መሪና ረዳት አሰልጣኝ አብርሃም መላኩ የውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት
ኮሚቴ ሊያነጋግራችሁ ስለሚፈልግ ሰኞ ግንቦት 2 /2013 ዓ.ም በ 4፡00 ሰዓት ሃዋሳ ዩኒቨርስቲ ስቴዲየም እንድተገኙ ጥሪ ተላልፏላቸዋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...