By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ለከሰሱት ጠበቆችና ለአራቱ ከሳሾች ማስጠንቀቂያ ሰጠ….
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችአትሌቲክስ

የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ለከሰሱት ጠበቆችና ለአራቱ ከሳሾች ማስጠንቀቂያ ሰጠ….

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 1 year ago
Share
SHARE

“ከሳሾች በውሸት ቃለመሀላ ፍርድ ቤቱን ያሳሳቱ በመሆናቸው ራሳቸው በህግ የሚጠየቁበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም”
የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ

 

“የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ምርጫ ታገደ ለሚባለው የደረሰን ነገር ባይኖርም በውሸት ቃለመሀላቸው የተሳሳተ ዳኛ ካለ በህግ አግባብ እናስቀለብሳለን” ሲል የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ዛተ።

ኦሎምፒክ ኮሚቴውን የከሰሱ ጠበቆች የሰጡትን መግለጫ ተከትሎ ኦሎምፒክ ኮሚቴው በሰጠው ባለ 6 አቋም የምላሽ መግለጫ “ከሁሉም በላይ እነዚህ ከሳሾች በውሸት ቃለመሀላ ፍርድ ቤት ያሳሳቱ በመሆናቸው ራሳቸው በህግ የሚጠየቁበት ጊዜ ሩቅ እንደማይሆን እንረዳለን ከዚህ ቀደም በኦሊምፒክ ኮሚቴ ውስጥ የስፖርት ትጥቆችን መርካቶ ድረስ ሄደው በመቸብቸብ በፈፀሙት ህገ ወጥ ተግባር በኮሚቴው የታገዱ አካላት ስልጣን በሌለው መደበኛ ፍርድ ቤት ከሳሽ ሆነው መቅረባቸውም እጅግ አሳፋሪ ነው ” ሲል የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ገልጿል።

- ማሰታውቂያ -

ኦሎምፒክ ኮሚቴውን የከሰሱ ጠበቆች የሰጡትን መግለጫ ተከትሎ ኦሎምፒክ ኮሚቴው በሰጠው መግለጫ ” የስፖርት ነክ ጉዳዮች በመደበኛ ፍርድ ቤት እንደማይታዩ እና መደበኛ ፍርድ ቤት ስልጣን እንደሌላቸው እየታወቀ ህግና ስርአትን ተከትሎ ጥያቄ ማንሳት ሲገባ የውሸት ቃለመሀላ በማቅረብ እና ተረኛ ችሎቱን በማሳሳት እግድ ያወጡበት መንገድ ከሳሽ ነን የሚሉት ግለሰቦች ተከራክረው ማሸነፍ የሚችሉበት የእውነተኛ የህግ መሰረት የሌላቸው መሆኑን ያሳያል። በተጨማሪም በውሸት ቃለመሀላ ያገኙትን እግድ ልክ ተከራክረው እንዳሸነፉ መግለጫ መስጠታቸው የቱን ያህል በሀላፊነት እና በተጠያቂነት ስሜት እንደማይሰሩ በግልፅ የሚያሳይ ነው። ሀገርን ለማስቀጣት የሚደረገው እንቅስቃሴ በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል” ሲል የትድረስ እንደሚሄድ አስጠንቅቋል።

በአለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ (IOC) ሙሉ በሙሉ የታገደውና እውቅና በግልፅ የተከለከለው እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አባል ያልሆነው በአቶ እያሱ ወሰን የሚመራው የቀድሞው የቦክስ ፌዴሬሽን ከሳሽ ሆኖ መምጣቱ ” እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ” እንዳለችው እንስሳ ኦሊምፒክ ኮሚቴን ይዤ ልውደቅ ከሚል ክፉ መንፈስ የመነጨ በመሆኑ ይህንን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲገነዘበው ለመግለፅ እንወዳለን” ያለው ኦሎምፒክ ኮሚቴው አንዳንድ የሚዲያ ባለሙያዎች ከግለሰቦች ጋር በግልፅ በገንዘብ በመደለል እና በጥቅም በመተሳሰር (ለዚህም በቂ ማስረጃዎች አሉ ) ለህብረተሰቡ የተዛቡ እና ሚዛናዊ ያልሆኑ የአንድ ወገንን መረጃ ብቻ በማቅረብ የስፖርት ቤተሰቡን እያሳሳቱት ይገኛሉ ከህገ ወጥ ድርጊታቸውም እንዲቆጠቡ እናሳስባለን” ብሏል።

“ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ የባለፉትን አራት አመታት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ምክትል ፕሬዝደንት ሆኖ ቆይቷል ነገር ግን ራሱን ከደሙ ንፁህ ነኝ በሚል እና ከዚህ ቀደምም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት በነበረበት ወቅት ለማናጀሮች እና ለስፖርት ትጥቅ አምራች ካምፓኒዎች አሳልፎ በመስጠት ብሄራዊ ቡድን ያፈረሰው ራሱ ሆኖ እያለ የስፖርቱ ተቆርቋሪ ሆኖ መምጣቱ እጅግ አሳዝኖናል ለመሆኑ ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ የባለፉትን አመታት የት ነበር ? ” ሲል የጠየቀው የኦሎምፒክ ኮሚቴ መግለጫ ጀግናው አትሌት ገዛኸኝ አበራ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት እንደሆነ ይታወቃል። በፌዴሬሽኑ ውስጥ ያለበትን የማኔጅመንት ክፍተት ወደ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ይዞ መምጣቱ ” ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ” የሚባለው ብሂል አይነት ነው” ሲል ተሳልቋል።

በዶክተር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ እየተካሄደ ያለውን ግልፅ ህገወጥ ተግባር የስፖርት ቤተሰቡ ግራ ቀኙን አገናዝቦ እንዲመለከተው ጥሪውን እናስተላልፋለን ብሏል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ላይ የቀረበው ክስ ዝርዝር ይፋ ሆነ….
Next Article የ2016ቱ የፕሪሚየር ሊግ ኮከቦች በቀጣይ ሳምንት ይፋ ሊደረጉ ነው….

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
English ArticleRecapETHEPL

Ethiopian Premier League Week 11 recap | Core Points, Results, Scores, and league standings

Muluken Tesfaye By Muluken Tesfaye 6 years ago
“ህጋዊ ተጨዋች መሆንን እፈልጋለው፤ አዲሱ ክለቤንም የዝውውር መስኮቱ ሲከፈት አሳውቃለው”ይሁን እንዳሻው
ሀትሪክ አበይት ጉዳዮች| የ10ኛ ሳምንት ዋና ዋና ጉዳዮች
የኢትዮጵያ ከ 23 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በወዳጅነት ጨዋታ አሸንፏል !
የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ የምድብ ለ የመጨረሻ ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ተደርገዋል ።
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?