By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ላይ የቀረበው ክስ ዝርዝር ይፋ ሆነ….
Share
Notification Show More
Latest News
ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ወልዋሎ ዜናዎች
ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ
ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ አዳማ ከተማ መቐለ 70 እንደርታ ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሲዳማ ቡና
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችአትሌቲክስ

የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ላይ የቀረበው ክስ ዝርዝር ይፋ ሆነ….

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 1 year ago
Share
SHARE

” ወደ 1 ቢሊዮን ብር ኦዲት አልተደረገም የት እንደገባ እንዴትስ እንደወጣም አይታወቅም”
ጠበቆቹ

” ስፖርቱን ላለፉት 35 አመት ለፍቼበታለሁ ገና እለፋለሁ ውስጤ ቁጭት እልህ አለ ስልጣን ግን በፍጹም አልፈልግም”
ጀግናው አትሌት ሻለቃ ሃይሌ ገ/ስላሴ

“ግለሰባዊ አጀንዳ የለንም ይሰቀል ይገደል የምንለው ሰውም የለም ከኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ጋር የገጠምነው ክርክር ዋናው ዓላማ ስፖርቱን ለመታደግ ብቻ ያደረግነው መሆኑ ታሳቢ እንዲደረግ እንጠይቃለን” ሲል ጀግናው አትሌት ሻለቃ ሃይሌ ገ/ስላሴ ተናገረ።

ከኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ጋር በተፈጠረው አለመግባባት ዙሪያ ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍ/ቤት የወሰዱት ጠበቆች ዛሬ በሃይሌ ግራንድ ሆቴል በሰጡት መግለጫ ላይ ኮከቡ አትሌት በሰጠው አስተያየት
” ስፖርቱን እንፈልገዋለን በኛ በኩል ለኦሎምፒክ ኮሚቴ ስልጣን ፍላጎት የለንም በዚህ ስፖርት ላለፉት 35 አመት ለፍቼበታለሁ ገና እለፋለሁ ውስጤ ቁጭት እልህ አለ . በፍጹም ግን ስልጣን አንፈልግም በግላችን ስፖርቱን ከመታደግ ውጪ አመራሮቹን የማሳጣት ፍላጎትንም የለንም ” ብሏል። እንደ ሃይሌ እምነት ” ኬንያ የወሰደችውን ርምጃ እንዲወሰድ የሚታሰር ሰው እንዲኖር አንፈቅድም ይህን ችግር ተሸክመንም ሎስ አንጀለስ መሄድ የለብንም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተፈጠረውን ችግር መፍታት ስላልቻለ ብቻ ነው ወደ ፍ/ቤት የሄድነው … በዚህ ጉዳይ መደበኛ ፍርድ ቤት በመሄድ የመጀመሪያ ባለሙያዎች ሳንሆን አንቀርም ይሄ በእውነት ያሸማቅቃል ” ሲል አስተያየት ሰጥቷል።

- ማሰታውቂያ -

ጠበቆቹ በበኩላቸው በሰጡት መግለጫ ” ከሳሾቹ የኢትዮጵያ ቴኒስ እና ቦክስ ፌዴሬሽኖች ሻለቃ ሃይሌ
ገ/ስላሴና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ም/ል ፕሬዝዳንት ገዛኧኝ አበራ መሆናቸውና እነሱን ወክለው ችሎት ላይ እንደሚቆሙ አስረድተዋል ። ” እንደ ቅደም ተከተላቸው የኢትየጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ እንደ ተቋም በግል ፕሬዝዳንቱ ዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ፣ ዋናና ምክትል ጸሃፊዎቹ አቶ ዳዊት አስፋውና አቶ ገዛኧኝ ወልዴ እንዲሁም ሃቃቤ ነዋይ ዶ/ር ኤደን አሸናፊ መከሰሳቸውን የገለጹት ጠበቆቹ አራት ፌዴሬሽኖች ክሱን ለመቀላቀል ጠይቀው ጉዳዩን እያዩ መሆናቸውን ይፋ አድርገዋል። ” አራት ፌዴሬሽኖች የዚህ ክስ አካል ለመሆን ጠይቀውናል እያጠናነው ነው ከማን ጋር ነው የምንጋጨው ብለው የሰጉም አሉ ማንም በህግ አንጻር እኩል ነው ብለን ነው የምናምነው የምንጋጨውም ግለሰብ የለም መንግስት ጣልቃ ይገባል ብለንም አንሰጋም” ሲሉ ተናግረዋል።

ጠበቦቹ አጽንኦት በሰጡት መግለጫቸው የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ኦዲት አልተደረገም ወደ 1 ቢሊዮን ብር በካሽና በአይነት ያለው ሂሳብ ኦዲት እንዲደረግ ጠይቀናል ወደ 48 ሚሊዮን ብር ለአኖካ ስብሰባ ተብሎ መንግስት ክፍያ ፈጽሟል እንደ ኢትዮ ቴሌኮምና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፍተኛ ክፍያ ፈጽመው ኦዲት አልተደረገም ከ400 ሺህ ዶላር በላይ የሆኑ ትጥቆች በየአመቱ ከአዲዳስ ይላካል የት እንደገባ አልታወቀም
ኦሎምፒክ በተደረገ ቁጥር ወደ 600 ሺህ ዶላር የሚገመት ትጥቅ ድጋፍ ይደረጋል ለመላው አፍሪካ ወደፐ 500 ሺህ ዶላር ድጋፍ ተደርጓል ለኦሎምፒክ ውድድር ተሳትፎ 30 ሺህ ዶላር ለስልጠና ተብሎ ከ15-20 ሺህ ዶላር በየአመቱ ይመጣል 198 ሺህ ዶላር ወጣቶችን ለማትጋት ተብሎ ይሰጣል እስካሁን ግን ምንም ኦዲት አልተደረገም ባህልና ስፖርት ሚኒስቴርም የሚጠበቅበት ሃላፊነቱን አልተወጣም በዚህም አዝነናል ዋናው ጥያቄያችን ከላይ የገለጽናቸው ገቢዎች የት ገቡ ወይም ለምን ወጪ ተደረጉ የሚለው ምላሽ ያስፈልገዋል ችሎቱን የጠየቅየውም ይህንን ነው ሲሉ አብራርተዋል።

ጠበቆቹ አቶ አያሌው ቢታኒ ፣ አቶ ሃይሉ ሞላና አቶ ጳውሎስ ተሰማ ለመደበኛ ችሎት አቀረብን ባሉት የክስ ማብራሪያ ግንቦት 5 እና ሰኔ 14/2016 የተደረጉት ህገወጥ ጉባኤና ውሳኔዎቹ ይሰረዙ፣ ተገቢ በሆነ አግባብ አጠቃላይ ወጪ ላይ ኦዲት ይደረግ በፓሪስ ኦሎምፒክ ህገወጥ የሰዎች ዝውውር እንደተካሄደ የሚያሳይ ነገር ስላለ በውጭ ጉዳይ ሚ/ር እና በፈረንሳይ ኤምባሲ በኩል እነማን ሄዱ እየማን ተመለሱ የሚለው እንዲጣራ ጠይቀናል ሲሉ አብራርተዋል። “ኦሎምፒክ ኮሚቴው በ64 ሚሊዮን ብር ወጪ የውሃ ማምረቻ ፋብሪካ ለማሰራት ማሽኖችን ከውጪ አስገብቷል የገቡት ማሽኖች እውነት ለፋብሪካው ስራ የሚጠቅሙ ናቸው የሚለው ይጣራል ሲሉም ገልጸዋል።

ለመንግስታዊ ተቋሙ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የሚጠበቅበትን ዳኝነት እንዲሰጥ በተደጋጋሚ ያቀረብነው ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ ባለማግኘቱ ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍ/ቤት እንደ ወሰዱት ያብራሩት ጠበቆቹ
ባህልና ስፖርት ሚ/ር መስሪያ ቤቱም ችሎቱ ፊት ቀርቦ ምላሽ ይሰጣል ለደረሰው ጉዳት ወጪ ይሸፍናል ሲሉ ተናግረዋል። በግልና በኦሎምፒክ ኮሚቴ አመራሮች ላይ የተወሰነው የ11 አካውንት እገዳ ጊዜያዊ ነው እገዳው እስከ ችሎቱ ውሳኔ የሚሰጥበት ጊዜ ድረስ የጸና ነው ” በማለትም ሂደቱን ገልጸዋል

ጠበቆቹ አጽንኦት ሰጥተው እንደገለጹት
“የሀገራችንን ስፖርት ለመታደግ በሚደረጉ ጥረቶች ላይ እንድንሳተፍ የተሰጠን እድል በመሆኑ ስራውን የምንሰራው በደስታ ነው ዋና አላማው የአገሪቱን የስፖርት ሀብት መታደግን ነው ግለሰቦች ተኮር አይደለም ውጤት ጠፍቷል ይሄ ደግሞ እንደ ዜጋ ያገባናል ውጤት ከጠፋ ድጋፎች ይቀንሳሉ ያለፉት ሶስት እሎምፒኮች ውጤት ደግም ለቀጣዩ ስላሰጋን ስፖርቱን ለመታደግ የሚደረገውን ጥረት ተቀላቅለናል” ሲሉ ገልጸዋል።

You Might Also Like

ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ

ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ

ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ

ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ

ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article ኢትዮጵያ የምትሳተፍበት የ20 ዓመት በታች አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የሴካፋ ዞን ድልድል ይፋ ሆነ
Next Article የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ለከሰሱት ጠበቆችና ለአራቱ ከሳሾች ማስጠንቀቂያ ሰጠ….

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችፋሲል ከተማ

የፋሲሉ ባህርዳር ከተማ ቡድን ወጥነት የለውም ብለው አስተያየት የሚሰጡት በራሳቸው ዱካ ውስጥ ሆነው ቢሆንም አሴተያየቱን አከብራለሁ

Yishak belay By Yishak belay 5 years ago
የዋልያዎቹ የማክሰኞ ጨዋታ የት ይካሄድ ይሆን ?
ሪፖርት | መከላከያ ኢትዮ-ኤሌክትሪክን በማሸነፍ የሊጉን ሁለተኛ ዙር በድል ጀምሯል።
ፋሲል ከተማ አሰልጣኝ ውበቱ አባተን አስፈርሟል
አህመድ ረሺድ እና ኢትዮጵያ ቡና ይለያዩ ይሆን??? ከአህመድ ረሺድ ጋር የተደረገ ቆይታ/EXCLUSIVE INTERVIEW/
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?