አሰልጣኝ በረከት ደሙ ከአርባምንጭ ከተማ ጋር ሲለያዩ የቀድሞው አንጋፋ ተከላካይ ቡድኑን ተቀላቅሏል።
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ ደካማ የውድድር ጉዞን እያደረጉ ከሚገኙ ቡድኖች መካከል አንዱ የሆነው አርባምንጭ ከተማ ትላንት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቡድኑ መረታቱን ተከትሎ ለአሰልጣኝ በረከት ደሙ ከሳምንታት በፊት የሰጠውን የሦስት ጨዋታዎች ዕድል ባለ መጠቀሙ ክለቡ ማሰናበቱን የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት ሀይለማርያም አረጋግጠውልኛል።
በሊጉ ከተደረጉ አስር ጨዋታዎች አምስት ተሸንፎ በአምስቱ አቻ ወጥቶ አንድም ጨዋታ ማሸነፍ ሳይችል በ5 ነጥብ በደረጃ ሰንጠረዡ 19ኛ ላይ ለመቀመጥ የተገደደው ክለቡ ለጥቂት ጨዋታዎች ቦቻ ቦታውን በጊዜያዊ የአሰልጣኝነት ማዕረግ አዲስ አሰልጣኝ እስኪሾም ድረስ የቀድሞው የአርባ ምንጭ ጨርቃጨርቅ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ የሱዳኑ አልሀሊ ሸንዲ ፣ ደቡብ ፓሊስ ፣ ወልቂጤ ከተማ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የግራ መስመር ተከላካይ እና በቅርቡ የፋስት ትራክ የቢ ላይሰንስ ባለቤቱ አበባው ቡጣቆ ቡድኑን በጊዜያዊ ስያሜ አሰልጣኝ (ማስተባበር) ስራን እንዲመራ ተመርጧል።



