መነሻ ገጽ ዋልያዎቹ የ25ቱ ጋዜጠኞች የካሜሩን ጉዞ ከሸፈ ተባለ
ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የ25ቱ ጋዜጠኞች የካሜሩን ጉዞ ከሸፈ ተባለ

አጋራ
አጋራ

ዋሊያዎቹ በካሜሩን ያውንዴ የሚያደርጉትን የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታዎችን ለመዘገብ ሙሉ ወጪያቸውን ተችለው ወደ ስፍራው ሊያቀኑ የነበሩ 25 ጋዜጠኞችን የመውሰድ ዕቅድ መክሸፉ ተነገረ።

ደጋፊዎችን ወደ ካሜሩን ለመውሰድ ሙሉ ሃላፊነቱን የተረከበው የሲሳይ አድርሴ ፕሮሞሽን ባለቤት አቶ ሲሳይ አድርሴ እንደገለጹት “ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመነጋገር 25 ጋዜጠኞችን ሙሉ ወጪ ተችሎ ወደ ካሜሩን የመውሰድ ዕቅዳችን የከሸፈው የራሳቸውን ጥቅም ባስቀደሙና ላንሄድ እንችላለን በሚል ስጋት ውስጥ የገቡ በጣት የሚቆጠሩ ራስ ወዳድ ጋዜጠኞች በሰሩት ተንኮል ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

እንደ አቶ ሲሳይ ገለጻ “ከራስ ጥቅም ይልቅ ለሀገራቸው እግርኳስ ቅድሚያ የሰጡና የሀገራቸውን እድገት የሚመኙ የስፖርት ጋዜጠኞችን ለማበረታታት ከፌዴሬሽኑ ጋር በመነጋገር ከፍተኛና የተሳካ የተባለ ስራ ስንሰራ ብንቆይም በስግብግብ ጋዜጠኞች ተንኮል ባለመሳካቱ አዝነናል። እነኚሁ ጋዜጠኞች ሀሰተኛ መረጃ ለስፖንሰር አድራጊዎቹ ተቋማት አመራሮች በመግለጽ በመሃላችን መተማመን እንዳይኖር አድርገዋል።

ፌዴሬሽኑና ሲሳይ አድርሴ ፕሮሞሽን በኛና በተቋማችን ላይ ማዘዝ አይችሉም እኛን ስፖንሰር አድርጉን በነሱ በኩል ምንም ጥቅም አታገኙም በሚል ተቋማቱ ላይ ጥያቄ እንዲጫር አድርገው ጋዜጠኞቹ ከየተቋማቱ ማረጋገጫ ደብዳቤ ካላመጡ ገንዘቡን አንፈቅድም በማለታቸው የተቋማቱን ስምምነት እንዲፈርሰ አድርገዋል። ከፌዴሬሽኑ ጋር በመነጋገርም ችግሩ ከአቅም በላይ መሆኑን በመረዳት ዕቅዳችንን ሙሉ በሙሉ ሰርዘናል።

የስፖንሰር አድራጊው ተቋም አመራሮች ደውለው የተፈጠረውን ችግር ሲገልጹ በቀጥታ የሰሙ ጋዜጠኞችም በተፈጠረው ነገር እነርሱም ተከፍተዋል” በማለት ሁኔታውን ገልጸዋል።

አቶ ሲሳይ በግላቸው ባገኙት ስፖንስር ወደ ካሜሩን የሚጓዙ አራት ጋዜጠኞችም እንዳሉ አስረድተው ደጋፊዎችን የመውሰዱ ሂደት ተጠናክሮ መቀጠሉን አሰረድተዋል። የፊታችን እሁድ ጥር 1/2014 በካሜሩን ያውንዴ የሚደረገው የአፍሪካ ዋንጫ ሲጀመር ምሽት 4 ሰአት ላይ ኢትዮጵያ ከኬፕቬርዴ ጋር በምታደርገው ጨዋታ በ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድቧን የመጀመርያ ጨዋታ ታደርጋለች ተብሎ እየተጠበቀ ነው።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...