*,,..አቶ በለጠ ዘውዴ በቃኝ ብሏል…
*….ፌዴሬሽኑ ጠቅላላ ጉባኤ ለማድረግ ለቅዳሜ ቀጠሮ ይዟል…
የአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን አንድ ከፍተኛ አመራር የሃላፊነት መልቀቅ ጥያቄ ማቅረባቸው እያነጋገረ ነው።
ከታማኝ ምንጭ በተገኘ መረጃ የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና በሲቲ ካፑ ስኬታማ ስራ የሰራው የህዝብ ግንኙነት ክፍሉ አቶ በለጠ ዘውዴ ከሃላፊነት የመልቀቅ ደብዳቤ ማስገባቱ ታውቋል።
አቶ በለጠ ደብዳቤ ካስገባ ነየቆየ ሲሆን ምክንያት የተደረገው ደግሞ የሚገባንን ስራ እየሰራን አይደለም በየጊዜው እየተገናኘም አንወያይም በዚህ አይነት አብሬ መወቀስ አልሻም በሚል እንደሆነ ታውቋል። ምክትል ፕሬዝዳንቷ አርቲስት ማስታዋል ወንደሰን በፌዴሬሽኑ ስራዋ ላይ ከተገኘች መቆየቷ ፕሬዝዳንቱን ተክታ መስራት አለመቻሏም ለአመራሩ የሃላፊነት መልቀቅ ጥያቄ እንደምክንያት መቅረቡ ታውቋል። ያም ሆኖ የአቶ በለጠ ደብዳቤ ከገባ ቢቆይም አመራሮቹ ጠርተው እንዳላናገሩት ታውቋል።
- ማሰታውቂያ -
የአዲስ አበባ እግርኳሰ ፌዴሬሽን ይፋ ባያደርገውም የጠቅላላ ጉባኤውን የፊታችን ቅዳሜ ከጠዌቱ 2.3ዕ በቸርችል ሆቴል ለማድረግ ቀጠሮ መያዙ ተሰምቷል
ጠቅላላ ጉባኤው ለሚዲያ ዝግ ይሁን አይሁን ግን እስካሁን የታወቀ ነገር የለም።


