….. ጉባኤውና ምርጫው ለሚዲያ ዝግ ነበር…..
….. ዶ/ር ወገኔ ባሉባት አርቲስቷ መመረጧ
የመራጮቹን አቅም ያስገመተ ሆኗል…..
….ኢኔጂነር ሃይለየሱሰ ወደሚያውቁት ቤት ዳግሞ ተመልሰዋል…
- ማሰታውቂያ -
…. ምርጫው 50+1 የሚለውን ባለሟሟላቱ እንደገና የተካሄደ ሆኗል….

የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ፌደሬሽን ጠቅላላ ጉባኤ አርቲስት ማስተዋል ወንደሰንን ም/ፕሬዘዳንት አርቲስት ሀረገወይን አሰፋን አቃቢ ነዋይ አድርጎ መምረጡ ይፋ ሆኗል።
የጠቅላላ ጉባኤው አባላቱ በግዮን ሆቴል
ባደረጉት ጉባኤና ምርጫ ከአራት አመት በፊት ፌዴሬሽኑን በፕሬዝዳንትነት የመሩትን ኢንጂነር ሃ/የሱስ ፍሰሃን ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል። ለፕሬዝዳንትነት ምርጫው ኢንጂነሩ 20 ተሸናፊው እጩ ፕሬዝዳንት ኢንስፔክተር የኔነህ 21 ድምጽ ያገኙ ሲሆን ከ44 መራጭ ድምጽ የ23ቱን ድምጽ ባለማግኘታቸውና ለሁለቱ እንደገና ድምጽ እንዲሰጥ ተደርጎ ኣንጂነር ሃ/የሱስ ገልብጠው ማሸነፍ ችለዋል። የእግርኳሱ ማህበረሰብ የሚያውቀው አንተነህ ፈለቀ ምርጫው ላይ የተሳተፈ ቢሆንም በሌለበት አንድ ድምጽ ብቻ ማግኘቱ ድምጽ የሰጡት እነማን ናቸው አስብሏል።
በዚህ ጉባኤ እነ ዶክተር ወገኔ ዋልታ ንጉስ የመሰሉ ባለሙያዎች ባሉበት ከፍተኛ የአመራር አቅም በሚጠይቀው ፕሬዝዳንቱ ከሌሉ ተክተው የሚሰሩበት የምክትል ፕሬዝዳንትነት ቦታን ለአርቲስት ማስተዋል ወንድወሰን ዓቃቤ ነዋይነቱን ለአርቲስት ሃረገወይን አሰፋ መስጠቱ ግምት ውስጥ የጣለው ሆኗል። ጉባኤው ላይ የነበረ ታማኝ ምንጭ እንደገለጸው አርቲስቶቹ የፌዴሬሽኑ ብራንድ ሆነው ከስፖንሰርሺፕ ጋር ተያይዞ ሊጠቅሙ እንደሚችሉ ነገር ግን የአመራር ሃላፊነት ቦታን ግን ካለባቸው የጊዜ እጥረትና የአቅም ውስንንነት አንጻር መመረጥም አልነበረባቸውም በማለት ድምጽ የነበራቸውን የክፍለ ከተሞቹን መራጮች ተችቷል። አርቲስት ማስተዋል ፕሬዝዳንቱ ኢኔጂነር ሃይለየሱስ በማይመኖሩበት ጊዜ ተክታ የመስራት ሃላፊነት ያለባት በመሆኑ የአርቲስቷን አመራር ሰጪነት ለማየት ብዙዎች ጓጉተዋል። የሴቶችን ተሳትፎ ለማስቀጠል ከማሰብ አንጻር ምርጫው ሴቶችን ማካተቱ ጥሩ ቢሆንም ጠንካራ አመራርነት ባለበት ቦታ ያለሙያ መመደብ ግን ተቀባይነት የሚያገኝ እንዳልሆነ ብዙዎች ይናገራሉ። በስራ አስፈጻሚ ምርጫ ላይ የኢትዮጲያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የቀድሞ የማርኬቲንግ ኮሚቴ ሃላፊ አቶ ኢሳያስ መመረጣቸውን ግን ምንጩ አወድሷል።
ጠቅላላ ጉባኤው ሲካሄድ ታይቶ በማይታወቅ ሂደት ለሚዲያ ዝግ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ከአዲስ ሚዲያ ውጪ አንድም ሚዲያ አለመኖሩ ጥያቄ አስነስቷል። የሀገሪቱ መዲና አዲስ አበባ እግርኳሷ ባላደገበትና ጭቅጭቅ በበዛበት ሂደት ጠንካራ አመራሮች ባለመመረጣቸው የከተማዋ እግርኳስ እድገት አይኖርም የሚል ስጋት ጭሯል። በዚህ ምርጫ ላይ አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ ለአመራርነት ተጠይቆ ፍቃደኛ ሳይሆን በመቅረቱ እነማስተዋልና ሀረገወይን መመረጣቸው ታውቋል። ይህም አንድም ቀን ባትሰራም ዘመኑን ጨርሶ በተሰናበተው ነባሩ አመራር የስራ ጊዜ ተመርጣ የነበረችው የኢትዮጵያ አይዶል ዳኛ አርቲስት ማህሌት ሌጋሲን የሚያስቀጥሉ አርቲስት አመራሮች ሆነዋል።
የጉባኤው አካሄድና ምርጫ የከተማ አስተዳደሩ ለእግርኳሱ አየሰጠ ካለው ትኩረትና ድጋፍ አንጻር የማይመጥን በመሆኑ የከተማ አስተዳደሩና የከተማው ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በጋራ ማስተካከያ እንዲደረግ ጫና ማድረግ እንዳለባቸው የስፖርት ቤተሰቡ እየጠየቀ ነው። በጉባኤው ላይ በአቶ ደረጄ አረጋ የሚመራው የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከአዲሱ አመራር ጋር ሙሉ ርክክብ ማድረጉ ታውቋል።


