መነሻ ገጽ ዜናዎች የአ/አ ዳኞችና ታዛቢዎች ማህበር ከ6 አመት በኋላ ዳግም ሊመሰረት ነው
ዜናዎች

የአ/አ ዳኞችና ታዛቢዎች ማህበር ከ6 አመት በኋላ ዳግም ሊመሰረት ነው

አጋራ
አጋራ

 

*… ባለፉት አመታት ማህበሩ ፍቃዱን አላሳደሰም….

የአዲስ አበባ ከተማ ዳኞችና ታዛቢዎች ማህበርን አጠናክሮ የባለሙያዎችን ጥቅም ማስከበር በሚችልበት አቅም ለማድረስ ያለመ የምክክር ጉባኤ በአዲስ አበባ ከተማ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ተካሄደ።

በአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ደረጄ አረጋ በተመራውና ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በዚህ የምክክር መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ዳኞችና ታዛቢዎች ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት ሚካኤሌ አርዓያ እንዲሁም የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት የማህበራት ማደራጃ ተወካይም ተገኝተው ማህበሩን ለማጠናከር በሚጠቅሙ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር አድርገዋል።

ማህበሩ ባለፉት ስድስት አመታት ፍቃዱን ሳያሳድስ ከመቅረቱም በላይ የከተማውን ዳኞችና ታዛቢዎችን ጥቅም ማስጠበቅ ያልቻለ፣ የማህበሩን ተልዕኮዎችና አላማዎችን ሳያስከብር የቆየ መሆኑን ተሰብሳቢዎቹ የተማመኑበት ሆኗል። ዳኞቹና ታዛቢዎቹ ባለፉት 6 አመታት የደረሰባቸውን መንገላታት በማስረዳት መብታቸውን የሚያስከብር ማህበር እንደሌላቸው በመግለጽ ለአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን ቅሬታ ማቅረባቸውን ተከትሎ ፌዴሬሽኑ በተለይ ደግሞ ፕሬዝዳንቱ አቶ ደረጄ አረጋ የቅድሚያውን ሀላፊነት በመውሰድ ውይይቱ መዘጋጀቱ ታውቋል።


ፌዴሬሽኑ ተበድለናል መብታችን አልተከበረም ካሉ ቅሬታ አቅራቢ ዳኞችና ታዛቢዎች ጋር ውይይቶችን አድርጎ ሰባት ተወካዮች የተመረጡ ሲሆን ፍቃዱን ሳያሳድሱ ባለፉት ዓመታት እንደ ማህበር ሲንቀሳቀሱና ማህበሩን ሲመሩ ከነበሩት አመራሮች ጋር ዛሬ ያደረጉት ውይይት ስምምነት ተደርሶበታል።

ውይይቱ ሲጠናቀቅ የአዲስ አበባ ከተማ ዳኞችና ታዛቢዎችን ህጋዊነት በመጠበቅና ጠንካራ ማህበር ለማቋቋም በመስማማት የተመረጡት አስተባባሪዎቹ ሁሉም የአዲስ አበባ ዳኞችና ታዛቢዎች እንዲገኙ ጥሪ በማድረግ ጥቅምት 20/2015 የምስረታ ጉባኤውን ለማካሄድ ወስነዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...