ከጥቅምት 12 እስከ 23 በሱዳን አስተናጋጅነት በሚካሄደዉ የሴካፋ ከ20 አመት በታች ዉድድር ላይ ለሚሳተፈዉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ከ20 አመት በታች ቡድን አሰልጣኞች ተሹመዋል።
የቀድሞዉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና በክለብ ደረጃ ደግሞ የኢትዮጵያ ቡና ፣ ባንኮች እና ኢትዮጵያ መድን ተጫዋች የነበረዉ እና ከ2014 የዉድድር አመት አንስቶ በንግድ ባንክ ከ20 በታች አሰልጣኝነት በመስራት ላይ የሚገኘዉ ዕድሉ ደረጀ በዋና አሰልጣኝነት ተሹሟል።
በተያያዘም በምክትል አሰልጣኝነት ደግሞ የቅዱስ ጊዮርጊሱ ሳምሶን ሙልጌታ እና የአዳማ ከተማዉ አፈወርቅ ከበደ ተሹመዋል።
- ማሰታውቂያ -
በዚህም ለ48 ተጫዋቾች ጥሪ መደረጉ ተገልጿል።