በሊጉ ደካማ የውድድር ጉዞን እያደረገ የሚገኘው መቐለ 70 እንደርታ በውጤት እጦት የተነሳ ዋና አሰልጣኙን አንስቷል።
በፕሪምየር ሊጉ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ከሰበሰቡት ተጫዋቾች አንፃር ጠንካራ ሆነው ይገኛሉ ተብለው ከሚጠበቁ ቡድኖች መካከል አንዱ የሆነው መቐለ 70 እንደርታ በሊጉ ቡድኑ ካደረጋቸው አስር ጨዋታዎች በ4 ነጥብ 20ኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን ተከትሎ በተደጋጋሚ ለአሰልጣኙ ከሰጠው ማስጠንቀቂያ በኋላ ማሰናበቱ ታውቋል።
መቐለን ወደ ፕሪምየር ሊጉ ከዚህ ቀደም ያሳደጉት እና በተጠናቀቀው የውድድር አመት ከከፍተኛ ሊጉ ወሎ ኮምቦልቻ በኋላ ስሑል ሽረን ያሰለጡትን አሰልጣኝ ጌታቸው ዳዊት ክለቡ የሰጣቸውን ዕድሎች አለመጠቀማቸው ለመለያየታቸው ምክንያት ነው ተብሏል።



