መቐለ 70 እንደርታ ከካኖ ስፖርት ሚያደርገው ጨዋታ ቀጥታ የቴሌቪዥን ሽፋን ሊያገኝ ነው
በክለቡ ታሪክ የመጀመርያ የሜዳው የካፍ ቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ ሚያደርገው መቐለ 70 እንደርታ ጨዋታው በቴሌቪዥን ሽፋን ሚያገኝበት እድል እግኝቷል።
በ2010 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የክለቡን የሜዳ ጨዋታዎች ቀጥታ ሲያስተላልፍ የነበረው ትግራይ ቴሌቪዥን እሁድ ነሐሴ 19 በቅርቡ በካፍ ፍቃድ ተሰጥቶት የመጀመርያ ኢንተርናሽናል ጨዋታውን በሚያስተናግደው ትግራይ ስታድየም ላይ ሚካሄደውን ጨዋታ በቀጥታ እንደሚያስተላልፍ አስታውቋል።
አስተያየት ይስጡ