የተጨዋቾች ውል በማራዘምና አዳዲስ ተጨዋቾችን በማስፈረም የተጠመዱት ፈሩሰኞቹ የክረምቱ ሥስተኛ ፈራሚያቸውን ከቢጫ ለባሾቹ ወልዋሎ አድርገዋል።በመቐለ 70 እንደርታ አሸናፊነት በተጠናቀቀው የ2011 ኢትዮጵያ ፕሪምየር ዘንድሮ ካሳያቸው ተስፈኛ ተጨዋች አንዱ የሆነው ደስታ ደሙ የፈረሰኞቹ የክረምቱ ሶስተኛ ፈራሚ በመሆን ተቀላቅሏል።
በብዙ ታላላቅ ክለቦች ሲፈለግ የነበረው ደስታ በዘንድሮ ዓመት ከወልዋሎ ውጪ ለኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ብሄራዊ ቡድን እና ለቻን ብሄራዊ ቡድን ተመርጦ መጫወት ችሏል።በተጨማሪም የኦሎምፒክ ቡድኑ አዲስ አበባ ላይ ማሊን በገጠመበት ጨዋታ በብሄራዊ ቡድኑ መለያ የመጀመርያ ግቡን ማስመዝገብ ችሏል።
በተያያዘ ዜና ጊዮርጊስ ቤትን ከተቀላቀለ 3 ዓመታትን የደፈነው አማካዩ ሙሉአለም መስፍን ከፈረሰኞቹ ጋር ለቀጣይ ሁለት ዓመታት ሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል።በ2009 ከሲዳማ ቡና ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ የፈረመው ጠንካራው የአማካይ ክፍል ተጨዋች ባለፋት 4 ዓመታት በብሄራዊ ቡድን አሰልጣኞች ጥሪ ቀርቦለት ሃገሩን በማገልገል ላይ ይገኛል።
የኢትዮጵያን በፕሪምየር ሊግን ካነሱ ሁለት ዓመታትን ያስቆጠሩት ጊዮርጊሶች የቀጣዩን ዓመት ዋንጫ ወደ ጊዮርጊስ ለማምጣት ከደስታ ደሙ በተጨማሪ የአብስራ ተስፋዬን እና እቤል እንዳለን ከደደቢት ሲያስፈርሙ፤ የአብዱልከሪም መሐመድ፣ሳላዲን በርጌቾ፣ለዓለም ብርሃኑ፣ጋዲሳ መብራቴ፣አሜ መሐመድ ና ናትናኤል ዘልቀን ውል ለሁለት ዓመት ማራዘማቸው ሚታወስ ነው።