By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሰፊ የግብ ልዩነት ማሸነፍ ሲችል ፤ ፋሲል ከነማም ወሳኝ ድል ተቀዳጅቷል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ወልዋሎ ዜናዎች
ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ አዳማ ከተማ መቐለ 70 እንደርታ ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ
ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሲዳማ ቡና
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ወልቂጤ ከተማየጨዋታ ዘገባፋሲል ከነማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወላይታ ድቻዜናዎችኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሰፊ የግብ ልዩነት ማሸነፍ ሲችል ፤ ፋሲል ከነማም ወሳኝ ድል ተቀዳጅቷል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ25ተኛ ሳምንት የመጀመሪያ ዕለት መርሐግብር የሊጉ መሪ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወላይታ ዲቻን 5ለ0 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

ቀን ዘጠኝ ሰዓት ሲል በጀመረዉ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታም የሊጉ መሪ ኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች ከጨዋታዉ መባቻ አንስቶ ብልጫ ወስደዉ ሲጫወቱ ገና በጊዜም በአማካዩ ሲሞን ፒተር እና የፊት መስመር ተጫዋቹ ኪቲካ ጀማ አማካኝነት ጥሩ የሚባሉ ሙከራዎችን አድርገዉ በ20ኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ ማስቆጠር ችለዋል።

በዚህም ሳይመን ፒተር ከግራ ወደ ውስጥ የላካትን ኳስ ተከላካዩ ፍፁም ግርማ በራሱ መረብ ላይ አሳርፎ ኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች ጨዋታዉን እንዲመሩ አስችሏል። ከዚች የመጀመሪያ ግብ መቆጠር በኋላ በተደጋጋሚ ብልጫ በመዉሰድ ሙከራዎችን ማድረግ የቀጠሉት ባንኮች ከዘጠኝ ደቂቃዎች በኋላም መሪነታቸዉን ወደ ሁለት ከፍ አድርገዋል። በዚህም ሳይመን ፒተር ከኋላ መስመር የተቀበለዉን ኳስ ለባሲሩ ዑመር አቀብሎት ተጫዋቹም ኳሷን በቀላሉ ወደ ግብነት ቀይሯል።

- ማሰታውቂያ -

በተደጋጋሚ የባንኮችን ሙከራዎች በመከላከል የጨዋታ ጊዜያቸዉን እያሳለፉ የነበሩት ዲቻዎች በ38ተኛዉ ደቂቃ ላይ በብዙዓሁ ሰይፉ አማካኝነት ብቻ ተጠቃሽ ሙከራ አድርገዉ ፤ በ44ተኛዉ ደቂቃ ላይ ደግሞ ግብ ሶስተኛ ግብ አስተናግደዉ አጋማሹ ተጠናቋል። በዚህም በተጠቀሰዉ ደቂቃ ኪቲካ ጀማ ከሱለይማን ሀሚድ የተሻገረለትን ኳስ ለሳይመን ፒተር አቀብሎት ተጫዋቹም ኳሷን በቀላሉ ወደ ግብነት ቀይሯል።

ከዕረፍት መልስ ይባስኑ ተጠናክረዉ የተመለሱት ተጠናክረዉ የተመለሱት ባንኮች በ55ተኛዉ ደቂቃ ላይ አራተኛ ግብ አስቆጥረዋል። በዚህም በዕለቱ ድንቅ የነበረዉ ሳይመን ፒተር ከኪቲካ ጀማ የተቀበለዉን ኳስ በቀኝ መስመር በኩል ለኤፍሬም ታምራት አቀብሎት ተጫዋቹም ኳሷን ወደ ግብነት መቀየር ችሏል። በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ ባንኮች በ77ተኛዉ ደቂቃ ላይ በኪቲካ ጀማ አማካኝነት አምስተኛ ጎል ማስቆጠር ችለዋል።

ደቂቃዉ የጨመረ በሄደ ቁጥር እንቅስቃሴዉ እየቀነሰ በቀጠለዉ ጨዋታ እጅግ ደካማ የነበሩት ዲቻዎች በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ በአበባየሁ ሀጂሶ እና ብዙዓሁ አማካኝነት ጥሩ ሙከራዎችን ማድረግ ቢችሉም ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ቀርተዉ 5ለ0 በሆነ ውጤት ተሸንፈዋል።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ፋሲል ከነማ ወልቂጤ ከተማን 1ለ0 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል ።

ምሽት 12:00 ሲል በዝናብ ታጅቦ በተከናወነዉ ጨዋታ ሜዳዉ ኳስን በነፃነት ለማንሸራሸር አስቸጋሪ ሆኖ የነበረ ሲሆን ፤ በዚህም በመጀመሪያዎቹ ጥቂት ደቂቃዎች በሙከራ ረገድም ሁለቱም ክለቦች ይህ ነዉ የሚባል ሙከራ ሳያደርጉ ቆይተዉ 15ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግን ግብ ተቀጥሯል። በዚህም በተጠቀሰዉ ደቂቃ የመስመር ተጫዋቹ ቃልኪዳን ዘላለም ከጋቶች የተቀበለዉን ኳስ ለጌታነህ ከበደ አቀብሎት ተጫዋቹም ኳሷን ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።

ከግቧ መቆጠር በኋላ በተደጋጋሚ በጥሩ የጨዋታ እንቅስቃሴ ወደ ተጋጣሚ ቡድን ሶስተኛዉ የሜዳ ክልል ይደርሱ የነበሩት ወልቂጤዎች አደጋዎችን በመፍጠር ረገድ ግን ደካማ ሁነዉ ግማሽ ሰዓት ያክል ተቆጥሯል። በዚህም በአጋማሹ በ30ኛዉ ደቂቃ ላይ ተመስገን በጅሮንድ ከርቀት ድንቅ ሙከራ ቢያደርግም የግብ ዘቡ ሚካኤል ሳማኬ ኳሷን አዉጥቷል። በዚህ ሁኔታ በቀጠለዉ ጨዋታ በአጋማሹ ተጨማሪ ሙከራ ሳይደረግ ክለቦቹ ለዕረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።

ከዕረፍት መልስ ሙሉዓለም መስፍን ከርቀት ወደ ግብ ልኳት ግብ ጠባቂዉ ሳማኪ እንደምንም ባወጣት ኳስ በጀመረዉ ሁለተኛዉ አጋማሽ በ60ኛዉ ደቂቃ ላይ ክትፎዎቹ ጌታነህ ከበደ ወደ ግብ የሞከራትን ኳስ የግብ ዘቡ መሳይ ሲመልስ ያገኘዉ ቃልኪዳን በድጋሚ ቢሞክርም ነገር ግን ተከላካዩ ወንድማገኝ አዉጥቶበታል።

በጨዋታዉ የመጨረሻ ደቂቃዎች ላይ የአቻነት ግብ ፍለጋ መታተር የቀጠሉት ወልቂጤዎች በአንድ ሁለት አጋጣሚ ዕድሎችን ማግኘት ቢችሉም መጠቀም ሳይችሉ ቀይተዉ በጨዋታዉ 1ለ0 በሆነ ዉጤት ተሸንፈዋል።

You Might Also Like

ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ

ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ

ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ

ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ

ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የፊዚዮቴራፒስቱ ይስሃቅ ሽፈራው የምስጋና ፕሮግራም ሊካሄድ ነው…
Next Article በፓሪስ ኦሎምፒክ የሚካፈለው የኢትዮጵያ የማራቶን ቡድን ይፋ ተደረገ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዋልያዎቹየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንዜናዎች

የኢትዪጵያ ከ 23 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በሰፊ ጎል አሸነፉ !

hatricksport team By hatricksport team 5 years ago
የግብፅ ብሔራዊ ቡድን ስብስብ ይፋ ሆኗል
የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ ደረጃቸዉን ማሻሻል የቻሉበት ዉጤት አስመዝግበዋል !!
 ዋና አሰልጣኝ ለመቀጠር ሲያመነታ የቆየው ወልዋሎ አዲግራት በመጨረሻም  አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያምን ቀጥሯል
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከኤልኔት ግሩፕ ድርጅቶች ጋር ለመስራት የስፖንሰር ሺፕ ስምምነት ፈጽሟል !!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?