መነሻ ገጽ ለገጣፎ ለገዳዲ የለገጣፎ ለገዳዲና የሊግ ኩባንያው አለመግባባት ከሯል
ለገጣፎ ለገዳዲመቻልቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የለገጣፎ ለገዳዲና የሊግ ኩባንያው አለመግባባት ከሯል

አጋራ
አጋራ

➡️ ጉዳዩ መንግስት ጋር ደርሷል…
➡️ የፌዴሬሽኑ ምላሽ እየተጠበቀ ነው…
➡️ መቻሎች ፎርፌ አግኝተዋል..

ለገጣፎ ለገዳዲ “በሊግ ካምፓኒው ዕገወጥ ድርጊትና የመብት ጥሰት እየተፈጸመብኝ ነው” ሲል ከሰሰ

ክለቡ ለኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በላከው ደብዳቤ “በሊግ ኩባንያው ተደጋጋሚ በደል ሲደርስብን እንደነበረና ፌዴሬሽኑ ህጋዊ ናቸው ያላቸውን ተጨዋቾች አልቀበልም በማለት በህገወጥ መንገድ የፌዴሬሽኑን ህግ ወደጎን በመተው የራሱን አቋም እያራመደ ቆይቷል” ሲል ከሷል።

ፌዴሬሽን ህጋዊ ናቸው ያላቸውን ተጨዋቾች ዝርዝር ለኛም ሆነ ለሊግ ኩባንያው ልኳል ያለው የክለቡ ደብዳቤ ሊግ ኩባንያው ህገወጥ ተግባሩን ማቆም አልቻለም ያም ሆኖ እኛ በተላከልን ህጋዊ ተጨዋቾች ዝርዝር መሠረት ወደ ጨዋታ ስናስገባ አወዳዳሪው አይቻልም ቢል በክለቡም ሆነ በክለቡ አባላት ላይ ለሚደርሰው ማንኛውም ችግር አወዳዳሪው አካል እንዲጠየቅልን እንፈልጋለን” ሲል ለፌዴሬሽኑ በጻፈውና በግልባጭ ለባህልና ስፖርት ሚኒስቴርና ለሚመለከታየው አካላት ባደረሰው ደብዳቤ ጠይቋል።

ምሽት ላይ ከድሬዳዋ በተሰማ ዜና ክለቡ ህጋዊ ናቸው ያላቸውን ተጨዋቾቹን ይዞ ወደ ሜዳ ሊገባ ሲል በአወዳዳሪ አካል የተከለከለ ሲሆን ለዲ ኤስ ቲቪ የደረሰው የሊግ ካምፓኒው ዝርዝር ህጋዊ ናቸው ያላቸው አራት ተጨዋቾች ብቻ መሆኑ አነጋጋሪ ሆኗል

የፌዴሬሽኑን የህጋዊነት ማረጋገጫ ቲሴራ ያገኙትን ተጨዋቾች ህጋዊ አይደሉም ብሎ ሊግ ካምፓኒው ሲከለክል የፌዴሬሽኑ አመራሮች ከመነጋገር ውጪ መብታቸውን ከማስከበር አንጻር ተገቢ ነው ያሉትን ርምጃ አለመውሰዳቸው እያነጋገረ ነው።

በሊግ ኩባንያውና በለገጣፎ ለገዳዲ አለመግባባት ዛሬ የነበረው ጨዋታ ያልተካሄደ ሲሆን መቻሎች 30 ደቂቃውን ጠብቀው ፎርፌ አግኝተው ከሜዳው ወጥተዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...

መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዘርአይ ሙሉ በቴክኒክ አማካሪነት ወደ ፕሪምየር ሊጉ ተመልሷል

አሰልጣኙን ያሰናበተው መቐለ 70 እንደርታ ሌላ ሹመትን ፈፅሟል። በያዝነዉ የዉድድር አመት ደካማ...