By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ሀዋሳ ከተማ ድል ሲቀናው መቀሌ 70 እንደርታ ከመቻል ነጥብ ተጋርተዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችሀዋሳ ከተማመቐለ 70 እንደርታሀዲያ ሆሳዕናየጨዋታ ዘገባመቻልየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የጨዋታ ዘገባ | ሀዋሳ ከተማ ድል ሲቀናው መቀሌ 70 እንደርታ ከመቻል ነጥብ ተጋርተዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎች በኋላ በዛሬው ዕለት በአራተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ሲመለስ ፤ ሀዋሳ ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 2 – 1 የረታ ሲሆን መቀሌ 70 እንደርታ ከመቻል ነጥብ ተጋርተዋል።

ከቀን 10:00 ጀምሮ በተደረገው የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ የዘርዓይ ሙሉው ሀዋሳ ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 2 – 1 አሸንፏል።

በጨዋታው ሀዋሳ ከተማ ገና በ8ኛው ደቂቃ ላይ በአቤኔዘር ዮሐንስ በተቆጠረ ግብ መሪ ሆኗል። አቤኔዘር ዮሐንስ ከሳጥኑ የቅርብ ርቀት የተገኘውን የቅጣት ምት በአስገራሚ ሁኔታ በቀጥታ ግብ አድርጎታል።

ሀይቆቹ መሪነታቸውን ከፍ ለማድረግ አራት ደቂቃዎች ብቻ ነበር የፈጁባቸው። ኤርትራዊው አጥቂ ዓሊ ሱሌማን በ12ኛው ደቂቃ ላይ የሀዋሳ ከተማን መሪነት ወደ 2 – 0 አሳድጓል።

- ማሰታውቂያ -

አጥቂው ከታፈሰ ሰለሞን በግሩም እይታ የደረሰውን ኳስ በተፈጥሯዊ ጠንካራ እግሩ በቀጥታ ወደ ግብ በመምታት ኳስ እና መረብን አገናኝቷል።

በሁለተኛው አጋማሽ 51ኛው ደቂቃ ላይ ፀጋአብ ግዛው ሀድያ ሆሳዕና ወደ ጨዋታው መመለስ የምትችል ግብ አስቆጥሯል። ከቅጣት ምት ወደ ግብ የተሻገረውን ኳስ የሀዋሳ ከተማ ተጫዋቾች በአግባቡ ለማራቅ በተቸገሩበት ወቅት ፀጋአብ ኳስና መረብን አገናኝቷል።

በመጨረሻም ሀዋሳ ከተማ 2 – 1 በማሸነፍ የውድድር ዓመቱን ሁለተኛ ድል ሲያሰመዘግብ ሀድያ ሆሳዕና ተከታታይ ሽንፈት ያስተናገደበት ሆኗል።

በአራተኛ ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው አርብ ጥቅምት 15 ሀዋሳ ከተማ አዳማ ከተማን ሲገጥም ፤ ሀድያ ሆሳዕና በበኩሉ ከሁለት ቀናት በኀላ ጥቅምት 17 ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ይጫወታል።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ከምሽት 1:00 ጀምሮ ጨዋታቸውን ያደረጉት መቀሌ 70 እንደርታና መቻል 1 – 1 በሆነ ውጤት ጨዋታቸውን አጠናቀዋል።

በጨዋታው 37ኛ ደቂቃ ላይ የመቀሌ 70 እንደርታው ያሬድ ብርሀኑ ቡድኑን ቀዳሚ ያደረገ ግብ አስመዝግቧል።

ከማዕዘን የተሻገረውን ኳስ በሌላኛው የቡድን አጋሩ ተገጭቶ ያገኘው ያሬድ ብርሀኑ በግንባር በመግጨት ግቡን አስቆጥሯል።

በሁለተኛው አጋማሽ 51ኛ ደቂቃ ላይ መቻል አቻ የሆነበት ግብ ተመዝግቧል። የመቀሌ 70 እንደርታው ዘረሰናይ ብርሀኑ ከመቻል ተጫዋች በረጅሙ ወደ መቀሌ 70 እንደርታ የግብ ክልል የተሻገረውን ኳስ ለማውጣት ሲጥር ተጨርፎበት በራሱ መረብ ላይ አሳርፎታል።

በመጨረሻም ጨዋታው በ1 – 1 ውጤት ፍፃሜውን አግኝቷል።

በአራተኛ ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ሀሙስ ጥቅምት 14 መቀሌ 70 እንደርታ ከድሬዳዋ ከተማ ሲጫወት ፤ በተከታዩ ቀን ጥቅምት 15 መቻል ከወልዋሎ አዲግራት ጋር ይገናኛል።

የሊጉ መርሐግብር በነገው ዕለትም ሲቀጥል ቀን 10:00 ጀምሮ ስሁል ሽረ ከድሬዳዋ ከተማ እንዲሁም ከምሽት 1:00 ጀምሮ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ሀድያ ሆሳዕና ከ ሀዋሳ ከተማ – ቅድመ ጨዋታ ቁጥራዊ መረጃዎች
Next Article አማኑኤል ገብረሚካኤል ወደ ጨዋታ ለመመለስ ተቃርቧል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
Uncategorized

የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ነገ አዲስ አበባ ይገባሉ

Mussie Girmay By Mussie Girmay 9 years ago
ሀትሪክ አሁንም ቀጠሮ ማክበር ስልጣኔ ነው በሚለው አቋሟ ጸንታለች
ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ | መቐለ 70 እንደርታ ከወልዋሎ አ.ዩ.
ሀትሪክ በነገው እትም ሳምንታዊዋ እና ተወዳጃ ጋዜጣዎ ሀትሪክ ነገ እናንተን በንባብ ታገኞታለች።
ባህርዳር ከተማ ከመመራት ተነስቶ አዳማ ከተማን ሲያሸንፍ ፤ ሀድያ ሆሳዕናም ከተከታታይ ሽንፈት በኋላ ወደ ድል ተመልሷል !!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?