ፋሲል ከነማ የተጫዋቹን ውል አራዝሟል !
በአሰልጣኝ ስዩም ከበደ የሚመሩት አፄዎቹ የግራ መስመር ተከላካያቸውን አምሳሉ ጥላሁን ( ሳኛን ) ውል ማራዘማቸው ተሰምቷል ።
በፋሲል ከነማ ክለብ በጠንካራ እንቅስቃሴዎቹ እና መሪነቱ የሚታወቀው አምሳሉ ጥላሁን በአፄዎቹ ቤት ለተጨማሪ ዓመት የሚቆይ ይሆናል ።
ከፋሲል ከነማ ወጣት ቡድን ጀምሮ መጫወት የቻለው አምሳሉ ጥላሁን በአውስኮድ ፣ ዳሽን ቢራ እንዲሁም ከ 2009 የውድድር ዓመት ጀምሮ አፄዎቹን በማገልገል ላይ ይገኛል ።