መነሻ ገጽ መከላከያ የ2010 የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ቀሪ ጨዋታዎች ከዛሬ ጀምሮ ይደረጋሉ።
መከላከያሲዳማ ቡናቅዱስ ጊዮርጊስኢትዮጵያ ቡናኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫጅማ አባጅፋር

የ2010 የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ቀሪ ጨዋታዎች ከዛሬ ጀምሮ ይደረጋሉ።

አጋራ
አጋራ

በ2010 መደረግ እና መጠናቀቅ እያለበት በተለያዩ ምክንያቶች እየተጎተተ እና እየተንከባለለ ወደ 2011 የተዛወረው የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ በሚደረግ 1 የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ የሚቀጥሉ ይሆናል።

በሀዋሳ አርቲፊሻል ስታዲየም በሚደረገው በዚህ ውድድር 5 ቡድኖች የቀሩ ሲሆን ዛሬ በሩብ ፍጻሜው ኢንተርናሽናል አርቢትር ለሚ ንጉሴ በሚመራው ጨዋታ 9:00 ሲል ቅ/ጊዮርጊስ ከሲዳማ ቡና የሚጫወቱ ይሆናል። በተጠናቀቀው የ2010 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለቱ ቡድኖች ተገናኝተው በሁለቱም ጨዋታዎች ቅ/ጊዮርጊስ በተመሳሳይ 1-0 በሆነ ውጤት አሸናፊ እንደነበር ይታወሳል። ቅ/ጊዮርጊስ ከ2006 ዓ.ም በኋላ ከአፍሪካ መድረክ ላለመራቅ እንዲሁም ሲዳማ ቡና ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ መድረክ ለመሳተፍ የዛሬውን ጨዋታ በማሸነፍ ጉዟቸውን ለማሳመር ከባድ ፉክክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የሁለቱ ቡድኖች አሸናፊ ማክሰኞ እለት በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ የ2010 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊውን ጅማ አባጅፋርን የሚገጥም ይሆናል። ጅማ አባጅፋር ለዚህ ግማሽ ፍጻሜ የበቃው ኢትዮ-ኤሌክትሪክን በፎርፌ በማሸነፍ እንደነበር ይታወሳል። በሌላ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ማክሰኞ ኢትዮጵያ ቡና ከመከላከያ የሚጫወቱ ይሆናል። የግማሽ ፍጻሜዎቹ አሸናፊ ሁለት ቡድኖች ደግሞ እሁድ መስከረም 20/2011 ዓ.ም ለፍጻሜ ተጫውተው አሸናፊው ቡድን በአፍሪካ ኮንፌደሬሽን ዋንጫ ኢትዮጵያን የሚወክል ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ፈረሰኞቹ ተጨማሪ ሁለት ተጫዋቾችን የግላቸው አደረጉ

ፈረሰኞቹ የሁለት ተጨማሪ ተጫዋቾችን ዝውውር አጠናቀቁ። በአሁኑ ሰዓት በሸራተን ሆቴል መግለጫ እየሰጡ...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ቅዱስ ጊዮርጊስ አራት ተጫዋቾችን የስብስቡ አካል ሲያደርግ የአማካዩ መፈረም አጠራጥሯል

በሰርቪያዊው አሰልጣኝ ጥቆማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ዝውውር ገብቷል። በቀጣዩ የውድድር ዘመን ሰርቪያዊውን...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ሰርቪያዊው ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ መጥተዋል

ከፈረሰኞቹ ጋር አምስት የፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ ያነሱት ሰርቪያዊው አሰልጣኝ ወደ ቀድሞው ክለባቸው...