መነሻ ገጽ Covid-19 የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል ተጨዋቾች ማህበር ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ያሰባሰቡትን ከ6 ሚሊየን ብር በላይ እርዳታ ዛሬ አስረከቡ
Covid-19ዜናዎች

የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል ተጨዋቾች ማህበር ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ያሰባሰቡትን ከ6 ሚሊየን ብር በላይ እርዳታ ዛሬ አስረከቡ

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል ተጨዋቾች ማህበር ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ይውል ዘንድ ከፕሪምየር ሊግ እና ከከፍተኛ ሊግ ቡድን ተጨዋቾች ያሰባሰቡትን ከ6 ሚሊየን ብር በላይ እርዳታ በዛሬው ዕለት ለድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ አስረክበዋል ።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት የመስተዳደሩ እና የስፖርት ኮሚሽን ከፍተኛ ሀላፊዎች እንደዚሁም ደግሞ የየክለቡ ካፒቴኖች እና የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል ተጨዋቾች አመራሮች በአዲስ አበባ ስታድየም በተገኙበት በእዚህ የገንዘብ ርክክብ ፕሮግራም ላይ ማህበሩ ይሄን ለወገን ደራሽ ወገን ነው በሚል መርህ ኮረና ቫይረስን መነሻ አድርጎ ለሰራው ስራ ከመስተዳደሩ ከስፖርት ኮሚሽንና ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከፍተኛ ምስጋና ቀርቦለታል።

የተሰባሰበውን ብርና ቁሳቁስ የኢ.ፊ.ዲ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ክቡር አቶ ኤሊያስ ሽኩር፤ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕረዚዳንት ክቡር አቶ ኢሳያስ ጅራ እና የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል ፋትቦለርስ አሶሴሽን ም/ፕሬዝዳንት አቶ መስፍን ብሩ በጋራ በመሆን ለአምባሳደር ምስጋናው አረጋ የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ አስረክበዋል ።
’’ድጋፉ በቀጣይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ክቡር አቶ ኤሊያስ ሽኩር እና አቶ ኢሳያስ ጅራ ጥሪያቸውን ሲያቀርቡ አምባሳደር ምስጋናው አረጋ በበኩላቸው ለተደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።

ክለቦቹ ተጫዋቾች እና አሰልጣኞች ያሰበሰቡት የገንዘብ መጠን ከታች የተቀመጠውን ምስል ይመልከቱ 👇

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...