የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ከ 17ኛው ሳምንት ጨዋታዎች በሃላ በአለም አቀፉ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መካሄድ ካቆመ ወራት ሊቆጠሩት ነው ::
ይህንንም ተከትሎ በሊጉ ቀጣይነት የተለያዩ መላ ምቶች እና አስተያየቶች ሲሰጡ ሰነባብተዋል ::
ይህንንም ተከትሎ በዛሬው እለት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ባስተላለፉት መልእክት የሊጉ ቀጣይነት ሳይሆን የሰው ህይወት ቅድሚያ እንደሚያሳስባቸው ገልፀው ጉዳዩ በግል የሚወሰን አለመሆኑን ተከትሎ ከሚመለከታቸው የፊፋ አካላት ጋር በመነጋገር የፊፋን አሰራር በመከተል በመጪዎቹ ቀናቶች በሊጉ ቀጣይነት ላይ ውሳኔ እንደሚተላለፍ ይፋ አድርገዋል ::