መነሻ ገጽ ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣ “ኢትዮጵያ ቡናዎች ካሳዬ አራጌ ለሚከተለው የጨዋታ ፍልስፍና ትሆናለህ ብለው ሲያመጡኝ ደስተኛ ሆኜ ነው የገባሁት” አለምአንተ ካሳ /ማሪዮ/ /ኢትዮጵያ ቡና/�
ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣዜናዎች

“ኢትዮጵያ ቡናዎች ካሳዬ አራጌ ለሚከተለው የጨዋታ ፍልስፍና ትሆናለህ ብለው ሲያመጡኝ ደስተኛ ሆኜ ነው የገባሁት” አለምአንተ ካሳ /ማሪዮ/ /ኢትዮጵያ ቡና/�

አጋራ
አጋራ

 



ሀትሪክ፡- ለኢትዮጵያ ቡና
ለመጫወት ፊርማህን አኑረሃል፤
ምን ስሜት ተሰማህ? ክለቡንስ
እንዴት የቅድሚያ ምርጫህ
አደረግክ?

አለምአንተ፡- ኢትዮጵያ ቡና
ለእኔ የመጀመሪያና ተቀዳሚ
ምርጫዬ ሊሆን የቻለው ክለቡ
በአገራችን የእግር ኳስ ታሪክ
በበርካታዎች ዘንድ የሚወደድና
የሚደገፍ ከመሆኑ ባሻገር የአዲስ
አበባም ክልል ቡድን ስለሆነ ነው፤
ከዛ ባሻገር ከአሜሪካ ሀገር ቡድኑን
ለማሰልጠን ለመጣው የአሰልጣኝ
ካሳዬ አራጌም የአጨዋወት ፍልስፍና
የአንተ እንቅስቃሴ አመቺ ነው
በሚልም ጥያቄ ስለቀረበልኝና
በቡድኑም ስለተፈለግኩኝ ቡናን
እንድመርጠውና ወደ ቡድኑ
በመግባቴም ደስተኛ አድርጎኛል፡፡

ሀትሪክ፡- ወደ ኢትዮጵያ ቡና
የአንተን አጨዋወት በመረዳት
እንድትመጣ ያደረጉህ አካላቶች
እነማን ናቸው?

አለምአንተ፡- ኢትዮጵያ ቡና በአሰልጣኝ
ካሳዬ አራጌ አማካኝነት ለሚከተለው የጨዋታ
ፍልስፍና አንተ ትሆናለህ በሚል ለክለቡ
እንድጫወት በመፈለግ እኔን ወደ ክለቡ
ያመጡኝ ሰዎች በምልመላው ላይ ቡድኑ
ኃላፊነት የሰጣቸው የአሰልጣኞች ስብስብ
ሲሆኑ ከእነዛም መካከል አሰልጣኝ ዘላለም
ፀጋዬ /ዞላ/ በዋናነት ይጠቀሳል፤ ከእነዚህ
መልማዮች ውጪም ከክለቡ ፕሬዝዳንት
መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞም ጋር ተነጋግረን
መግባባት ደረጃ ላይ ስለደረስን በእዚሁ ደረጃ
ወደ ቡና ልገባ ችያለው፡፡

ሀትሪክ፡- ስለ አሰልጣኝ ካሳዬ አራጌ
የጨዋታ ፍልስፍና ምን የምታውቀው ነገር
አለ? አሰልጣኙንስ ታውቀዋለህ?

አለምአንተ፡- የኢትዮጵያ ቡና የቀድሞ
ተጨዋችና አሰልጣኝ የሆነውን ካሳዬ አራጌን
ሲጫወትና ሲያሰለጥን በታሪክ ስለ እሱ
ሰማው እንጂ እኔ ፈፅሞ አልደረስኩበትም፤
የእሱን የጨዋታ ፍልስፍና በተመለከተ ከብዙ
ሰዎች ጥሩ ጥሩ ነገሮችን ማድመጥ ችያለው፤
ሲያሰለጥን አንድ ተጨዋች ባለው ነገር ላይ
ሰርቶ ችሎታውን የሚያሳድግበትን እንቅስቃሴ
እንደሚከተልና ተጨዋቹ የሌለውን ነገር
ደግሞ በጊዜ ሂደት እንዲያመጣ የሚያደርግ
በፓሲንግ ፉትቦልና ወደ ቶታል ፉትቦልምየሚያመራ ስልጠናን እንደሚሰጥ ተረድቻለ
ውና ይሄንን እኔ በመልካም ሁኔታ ልቀበለ
ውና በቡናም ጥሩ የውድድር ጊዜን ለማሳለፍ
ተዘጋጅቻለው፡፡

ሀትሪክ፡- ለኢትዮጵያ ቡና ከረጅም
ዓመታት እና ከእነ ዮሴፍ ተስፋዬ፣ ዓሊ
ረዲ፣ ካሊድ መሐመድ፣ ዑመር አብደላ፣
ቴዎድሮስ ብርሃኑና መሰል ተጨዋቾች
በኋላ አንተ ከኳስ ሜዳ አካባቢ በመውጣት
ለክለቡ ልትጫወት ተዘጋጅተሃል፤በዚህ ዙሪያ
የምትለው ነገር ካለህ…?

አለምአንተ፡- የእውነት ነው የአሁን
ሰዓት ላይ ኳስ ሜዳ ተጨዋቾች በጠፉበት
ሰዓት እኔ ከላይ ከጠቀስካቸው ተጨዋቾች
በኋላ ለኢትዮጵያ ቡና ለመጫወት ፊርማዬን
ማኖሬ በጣም ነው ደስ ያለኝ፤ አሁን ላይ
በትልቅ ቡድን ደረጃ ከአካባቢያችን ኳስን
የምንጫወተው ከሶስት አንበልጥም፤ ይሄ
ሁኔታ የቁጭት ስሜት ቢፈጥርብኝም እኔ
ደግሞ ኢትዮጵያ ቡናን በሚያህል ቡድን
ተፈልጌ ለክለቡ ልጫወት ዝግጁ መሆኔ ዕድለኛ
ከመሆኔ ባሻገር ከፍተኛ የደስታ ስሜትም ነው
በውስጤ እየፈጠረብኝ የሚገኘው፡፡

ሀትሪክ፡- ወደ ኢትዮጵያ ቡና ስታመራ
በየትኛው ሊግ ላይ እንደሚጫወት አውቀህ
ነው?

አለምአንተ፡- ኢትዮጵያ ቡና በየትኛውም
ሊግ ላይ ይጫወት ቡድኑ የእኔ የቅድሚያ
ምርጫ ሊሆን ችሏል፤ ከዛ ውጪ ሌላው ነገር
እኔን አያስጨንቀኝም፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...