መነሻ ገጽ Uncategorized ትግራይ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ተፈላሚዎቹን አሳውቋል
Uncategorizedመቐለ ከተማሽረ እንዳስላሴትግራይ ዋንጫአክሱም ከተማወልዋሎዜናዎችደደቢት

ትግራይ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ተፈላሚዎቹን አሳውቋል

አጋራ
አጋራ

መስከረም 26 ጅማሬውን ያደረገው ትግራይ ዋንጫ ትላንት በተካሄዱ ሁለት ጨዋታዎች የምድብ ጨዋታዎችን በማጠናቀቅ ወደ ግማሽ ፍፃሜ ያለፋትን አራት ክለቦች አሳውቋል።በዚህም መስረት ከምድብ ‘ሀ’ ሽረ እንዳስላሴ ና ደደቢት ከምድብ ‘ለ’ መቐለ 70 እንደርታ ና ድሬዳዋ ከተማ ማለፋቸውን ሲያረጋግጡ አክሱም ከተማ ወልዋሎ ዓ/ዩኒቨርሲቲ ከውድድሩ ተሰናብተዋል።

ሽረ እንዳስላሴ 2-1 ደደቢት

8 ሰዓት ላይ የተጀመረው የደደቢት ና የሽረ እንዳስላሴ ጨዋታ በሽሬ እንዳስላሴ አሸናፊነት ተጠናቋል።መሃል ሜዳ ላይ በሚቀባበሉ ኳሶች ትኩረት ያደረገው የመጀመርያ 45 ደደቢቶች የተሻለ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ቢያሳዩም ወደ ሜዳው የመጨረሻ ክፍል በሚሄዱበት ጊዜ የመናበብ ችግር ታይቶባቸዋል።ሽሬዎች በ3-5-2 አሰላለፍ ወደ ሜዳ ቢወርዱም መሃል ላይ የተሰለፋት ሳሙኤል ተስፋይ፣ሄኖክ ካሳሁን እና ሰለሞን ገ/ማርያም የቡድኑን ማረጋጋት ተስኗቸው ኳስ ቁጥጥር በደደቢት ብልጫ ተወስዶባቸዋል።በሁለተኛው አጋማሽ በሁለቱም ቡድን የተጫዋች ለውጥ በማድረግ የተሻለ ተንቀሳቅሰዋል።

ግብ የማግባቱን ቅድሚያ የወሰዱት ደደቢቶች ውድድሩ ላይ ጥሩ እየተንቀሳቀሰ በሚገኘው አለምአንተ ካሳ ኣማካኝነት ነበር።ከግቡ መቆጠር በኃላ ጫና መፍጠራቸውን የቀጠሉት ሽሬዎች በኣራት ደቂቃ ውስጥ በንስሃ ታፈሰና በሰይድ ሃሰን ኣማካኝነት ባስቆጠሩት ግቦች ታግዘው ጨዋታውን አሸንፈው መውጣት ችለዋል።

ድሬዳዋ ከተማ 1-1 ኣክሱም ከተማ

10 ሰዓት ላይ የተካሄደው የድሬዳዋና የአክሱም ጨዋታ ጥሩ ፋክክር የታየበት ነበር።ሁለቱም ቡድኖች በ4-2-3-1 ኣሰላለፍ የገቡ ሲሆን በመጀመርያው አጋማሽ ውድድሩ ላይ ጥሩ ብቃት እያሳዩ ሚገኙት በጌታቸው ዳዊት እሚመሩት አክሱሞች ጥሩ መንቀሳቀስ ችለዋል።በተለይ መሃል ሜዳ ላይ የተሰላፋት ስለሺ ዘሪሁን እና ትእዛዙ ፍቃዱ ቡድኑን ሚዛኑን ጠበቆ እንዲጫወት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርገዋል።ድሬዎችም የቆሙ ኳሶችን በመጠቀም የግብ እድሎችን መፍጠር ችለዋል።

በሁለተኛው አጋማሽ ጫና መፍጠራቸውን የቀጠሉት አክሱሞች በ56 ደቂቅ ላይ ያገኙትን ፍፁም ቅጣት ምት ልዑልሰገድ ኣስፋው አስቆጥሮ አክሱምን መሪ ማድረግ ችሏል።ከግቡ መቆጠር በኃላ ድሬዎች በሙሉ ሃይላቸው ጫና መፍጠር ሲጀምሩ አክሱሞችም በመልሶ ማጥቃት እድሎችን መፍጠር ችለዋል።በ85 ደቂቃ ሲላ ኣብዱላሂ ባስቆጠረው ግብ ድሬዎች ውድድሩ ላይ መቆየታቸውን አረጋግጠዋል።

የትግራይ ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች

አርብ ጥቅምት 2 ቀን 2011

8:00 ሽሬ እንዳስላሴ ከ ድሬዳዋ ከተማ

10:00 መቐለ 70 እንደርታ ከ ደደቢት

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...