መነሻ ገጽ ሪፖርት ሪፖርት | ቅዱስ ጊዮርጊስ አሁንም በሜዳው ሀያል መሆኑን አስመስክሯል።
ሪፖርትቅዱስ ጊዮርጊስድሬዳዋ ከተማ

ሪፖርት | ቅዱስ ጊዮርጊስ አሁንም በሜዳው ሀያል መሆኑን አስመስክሯል።

አጋራ
አጋራ

በደጋፊዎች ውብ ህብረ ዝማሬ የተጀመረው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ በሜዳው እና በደጋፊዎቹ ፊት በሊጉ ያለመሸነፍ ጉዞዎን ለማስቀጠል እንዲሁም ድሬድዋ ከተማ ከሽንፈት ለማገገም ያደረጉት ጨዋታ ነበር ::

ከጨዋታው ጅማሮ በፊት የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ አሰልጣኝ ሰርጆቪች ሚቾ በስታዲየም ሲገኙ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል ::

ጨዋታው እንደተጀመረ ፈጣን ምላሽ የሰጡት ፈረሰኞቹ በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች ላይ ከቀኝ መስመር ጋዲሳ ያሻማውን ካስ ጌታነህ ከበደ ከመረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል ::

ከጎሉ መቆጠር በሃላ ጫና ፈጥረው መጫወት የቀጠሉት ፈረሰኞቹ ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ቢያደርጉም ወደ ግብነት መቀየር ሳይችሉ ቀርዋል ::

ድሬድዋ ከተማዋች በኤልያስ ማሞ የመሀል ክፍሉን ብልጫ መውሰድ ቢያስቡም በመልሶ ማጥቃት መጫወት ምርጫቸውን አድርገዋል ::

ሙከራዎችን ማድረግ የተሳናቸው ድሬዳዎች በአንድ አጋጣሚ በቅጣት ምት ሞክረው ባህሩ ነጋሽ ካደነባቸው ሙከራ ውጪ አስደንጋጭ ሙከራ ሲያደርጉ አልተስተዋለም ::

በመጀመሪያው አጋማሽ መጠናቀቂያ ላይ ሳላህዲን ሰኢድ ባጋጠመው ጉዳት ሳቢያ ከሜዳ ተቀይሮ ሊወጣ ችሏል።

በመጀመሪያው አጋማሽ ሳልሀዲንን በጉዳት ያጡት ፈረሰኞቹ አቤል እንዳለን ቀይረው በማስገባት የሁለተኛውን አጋማሽ ጀምረዋል ::

በሁለተኛው አጋማሽ ጅማሮ ላይ ተጭነው የተጫወቱት ጊዮርጊሶች በእለቱ ድንቅ እንቅስቃሴን ሲያደርጉ ባመሹት ጌታነህ ከበደ እና ጋዲሴ መብራቴ በደቂቃዎች ልዩነት አከታትለው ባስቆጠራቸው ጎሎች የጎሉን መጠን ከፍ ማድረግ ችለዋል ::

ከጎል መቆጠር በሃላ ካስን በመያዝ አፈግፍገው የተጫወቱት ቅዱስ ጊዮርጊሶች ለድሬድዋ ከተማ ምቹ ሆኖ ተስተውላል ::

ድሬድዋዎች ከሶስተኛው ጎል መቆጠር በሃላ ወደ ጨዋታው የተመለሱበትን ጎል በድሬድዋ በኩል ጥሩ የሚባል እንቅስቃሴን ሲያደርግ የቆየው ሪችሞንድ ኦዶንግ ባስቆጠራት ግብ ወደ ጨዋታው ለመመለስ ጥረት አድርገዋል ::

ለፈረሰኞቹ አሳሳቢ እየሆነ በመጣው የጉዳት ዜና በሁለተኛው አጋማሽ ላይ ሌላኛው አጥቂያቸው ጌትነህ ከበደ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ከሜዳ ሊወጣ ችሏል።

ከጎሉ መቆጠር በሃላ ጫናዎችን ለመፍጠር የሞከሩት ድሬድዋዎች በተደጋጋሚ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል ሲደርሱ ተስተውላል ::

በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ የተዘናጉ የሚመስሉት ፈረሰኞች በጭማሪ አራት ደቂቃዎች ላይ ጎል አስተናግደዋል ::

ድሬድዋዎች ከሽንፈት ያልታደገች ጎል በሙህዲን ሙሳ አማካኝነት አስቆጥረዋል ::

ጨዋታው በቅዱስ ጊዮርጊስ አሸናፊነት ሲጠናቀቅ በደረጃው ሰንጠርዥ አራተኛ ሲቀመጡ በጨዋታው ሽንፈት ያስተናገዱት ድሬድዋዎች በወራጅ ቀጠናው ውስጥ ለመቆየት ተገደዋል ::

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ሰርቪያዊው ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ መጥተዋል

ከፈረሰኞቹ ጋር አምስት የፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ ያነሱት ሰርቪያዊው አሰልጣኝ ወደ ቀድሞው ክለባቸው...

ቅዱስ ጊዮርጊስኢትዮጵያ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

52ኛው የሸገር ደርቢ በቡናማዎቹ አሸናፊነት ተጠናቋል

በሀገሪቱ እግር ኳስ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የሸገር ደርቢ ኢትዮጵያ ቡና 3ለ1 በሆነ...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በቢጂአይ ኢትዮጵያ ስፖንሰር ሊደረግ ነው

ቅዱስ ጊዮርጊስ ከቀድሞው አጋሩ ጋር በድጋሚ ለመጣመር ውይይት አድርጓል። አንጋፋውን የቅዱስ ጊዮርጊስን...