ሀትሪክ ስፖርት፣ ሀትሪክ ስፖርት፣ ሀትሪክ ስፖርት በነገው እትሟ
ባለቀለሟ፣ ሳምንታዊዋ እና ተወዳጇ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ነገም የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የባህር ማዶ መረጃዎችን ይዛ በመውጣት እናንተን ውድ አንባቢዎቿን ታገኛለች፡፡
ሀትሪክ ስፖርት ነገ ምን ምን ጉዳዮችን ይዛሎት ትቀርብ ይሆን?
በሀገር ውስጥ የብዙዎችን አንባቢዎች ትኩረት በሳበው THE BIG INTERVIEW አምድ ታዋቂው አትሌት ሙክታር እንድሪስ ከሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ኤክስኪዩቲቭ ኤዲተርና ጋዜጠኛ ከሆነው ይስሃቅ በላይ ጋር በስፖርቱ ዘርፍና አዝናኝ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ ቆይታን አድርገው ለተጠየቀው ጥያቄ ምላሽ ሰጥቷል፤ ሀትሪክ በሌላ የሀገር ውስጥ ዘገባዋ በቻን አፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታ ሽንፈትን ስላስተናገደው የብሔራዊ ቡድናችንና ሌሎችንም መረጃዎች ከጋዜጣው ላይ ያገኙታልና የነገው ሀትሪክ አታምልጦት፡፡
ሀትሪክ ስፖርት በባህር ማዶ ዘገባዋም በዘንድሮ የፕሪምየር ሊጉ የእስካሁን ጉዞው በመቶ ፐርሰንት የማሸነፍ ሪከርድ ሊጉን እየመራ ስላለው እና በተጠባቂው የሳምንቱ ጨዋታ ቼልሲን ስላሸነፈው ሊቨርፑል እንደዚሁም ደግሞ አንድ ተጨዋች ከሜዳ በቀይ ካርድ ወጥቶበት ከኋላ በማንሰራራት ድል ስለቀናው አርሰናልና ስለ ቡድኑ ተጨዋች ኤምሪክ ኦቦሚያንግ፤ ከዛ ውጪም በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጥሩ ብቃትን እያሳዩ ስላሉ ወጣት ተጨዋቾችና ሌሎችንም ጨምረን እናንተን በንባብ ለማስደሰት ተዘጋጅተናል፡፡
ሀትሪክ የእርሶዎ ናት፡፡
የሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ የፊት ለፊት ገፅ ይህንን ይመስላል
አስተያየት ይስጡ