እዲሱ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፎርማት ተግባራዊ ሚሆን ከሆነ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተሳታፊ የመሆን አድል ያለው ደደቢት የአራት አዳዲስ ተጨዋቾች ዝውውር ማጠናቀቁን አስታውቋል።
አሰልጣኝ ጌታቸው ዳዊትን በሀላፊነት የሾሙት ደደቢቶች ባሳለፍነው የውድድር አመት ከወልዋሎ ጋር ቆይታ ያደረገው የቀድሞ የአልመዳ ጨርቃ ጨርቅ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣መቐለ 70 አንደርታ የቀኝ ተመላላሽ ዳንኤል አድሃኖም ሰማያዊዎቹን መቀላቀል ችሏል።
በተያያዘ ዜና ደደቢቶች ግብ ጠባቂ ሃብቶም ቢሰጠኝን ከስሑል ሽረ አስፈርመዋል።የትራንስ ኢትዮጵያ ወጣት ቡድን ውጤት የሆነው ሃብቶም ቢሰጠኝ ከዚህ ቀደም በሃዋሳ ከተማ፣መቐለ 70 አንደርታ፣ኣክሱም ከተማ፣ስሑል ሽረ መጫወቱ ሚታወስ ነው።
በተጨማሪ ደደቢት ክብሮም ግርማይ እና ክፍሎም ሓጎስን ከአክሱም ከተማ አስፈርመዋል።
አስተያየት ይስጡ