ወላይታ ድቻ ሁለት የውጪ ዜጋን ጨምሮ በድምሩ ሦስት ተጫዋቾችን ነገ ያስፈርማል።
የፕሪምየር ሊጉን የመጀመሪያ ዙር ወራጅ ቀጠና ውስጥ ሆኖ የቋጨው ወላይታ ድቻ በሁለተኛው ዙር በሊጉ ለመቆየት ይረዳው ዘንድ ከሳምንታት በፊት ሴኔጋላዊውን የ29 አመት ግብ ጠባቂ ከሀዲም ኒዲያዬን በነፃ ዝውውር የግላቸው በማድረግ የውጪ ተጫዋችን ዳግም ወደ ክለቡ ያመጣ ሲሆን በነገው ዕለት ደግሞ ናይጄሪያዊ አጥቂ እና ጋናዊ የአማካይ ስፍራ ተጫዋችን እንዲሁም ከከፍተኛ ሊግ አንድ ተካላካይን በድምሩ ሦስት ተጫዋቾችን በነገው ዕለት እስከ አመቱ መጨረሻ ድረስ እንደሚያስፈረም ያገኘሁት መረጃ አመላክቷል።
የተጫዋቾቹን ስም ዝርዝር እና ሌሎች መረጃዎችን በቀጣይ ይዤ የምንመለስ ይሆናል።



