በዝዉዉር ገበያው ላይ በንቃት በመሳተፍ የተለያዩ አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ስብስባቸዉ በመቀላቀል ላይ የሚገኙት ድቻዎች አሁን ደግሞ አማካዩን አዲስ ህንፃ ማስፈረማቸዉ ተረጋግጧል።
የቀድሞዉ የኢትዮጵያ መድን ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደደቢትን ከለቀቀ በኋላ ረዘም ያሉ አመታትን በአዳማ ከተማ ቤት መጫወት የቻለዉ አማካዩ በዉድድር አመቱ የቀድሞ አሰልጣኙን አሸናፊ በቀለን በመከተል ወደ ሀድያ ሆሳዕና ማምራቱ ይታወሳል።
የዉድድር አመቱን በሀድያ ሆሳዕና ቤት በጥሩ ብቃት ማጠናቀቅ የቻለዉ የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች አዲስ ህንፃ ከአንድ አመት የሀድያ ቆይታ በኋላ ወደ ወላይታ ድቻ መዘዋወሩ እርግጥ ሆኖአል።
አስተያየት ይስጡ