መነሻ ገጽ ኢትዮጵያን በውጪ “ከክለቡ ጋር ስለ መለያየት ያወራነው ነገር የለም” አሰልጣኝ ውበቱ አባተ
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

“ከክለቡ ጋር ስለ መለያየት ያወራነው ነገር የለም” አሰልጣኝ ውበቱ አባተ

አጋራ
አጋራ

የአሰልጣኝ ውበቱ አባተ እና የደቡብ ሱዳኑ ክለብ ዕጣ ፈንታ ምን ይሆን ?

ኢትዮጵያዊው አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከላይቬሪያው ክለብ ሊስከር የጥቂት ጊዜያት ቆይታ በኋላ ወደ ደቡብ ሱዳን አምርተው ጃሙስን ክለብን ሲያሰለጥኑ ቆይተዋል። የቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ ደደቢት ፣ ሀዋሳ ከተማ እና ፋሲል ከነማ አሰልጣኝ የነበሩት አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ቆይታ በኋላ በፋሲል ከነበራቸው ቆይታ መልስ ወደ ደቡብ ሱዳን እንዳመሩ ይታወሳል። የደበብ ሱዳኑን ክለብ ጃሙስን ብራዚላዊውን ሪካርዶን ተክተው በአንድ አመት ውስጥ አምስተኛ አሰልጣኝ መሆን ችለው የነበሩት ኢትዮጵያዊው ሰው በቅርቡ በደቡብ ሱዳን ፕሪምየር ሊግ ከሜዳቸው ውጪ ያስተናገዱት ሽንፈትን ተከትሎ ቀሪ ጨዋታዎች በሊጉ እየቀረ ኤልሜሪክ ቦንቱ ክለብ ቻምፒዮን መሆኑ ይታወሳል።

በሀገሪቱ ሊግ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው የአሰልጣኝ ውበቱ አባተው ክለብ ባለቤት በተደጋጋሚ በግሉ በሚወስናቸው ውሳኔዎች የተነሳ የሚፈልጓቸውን ተጫዋቾች ማምጣት እንዳልቻሉ በነበረኝ ቆይታ የገለፁልኝ አሰልጣኙ በአሁኑ ሰዓት ክለቡ በዛው ሀገር ባሉ አሰልጣኞች መሰልጠን የጀመረ ሲሆን አሰልጣኙ በስራ ላይ አመሆናቸውን ጠቁመውናል። አሰልጣኙ በስልክ እንዳሉኝ ከሆነም ቀሪ ኮንትራት ሰሰላለኝ ከክለቡ ጋር ቁጭ ብለን ስለመለያየትም ሆነ ስለሌሎች ጉዳዮች ያወራነው ነገር የለም ያሉኝ ሲሆን አሰልጣኙ እና በረዳት አሰልጣኝነት የወሰዷቸው ፋንታዬ አባተ እና መብራሀቱ ሀብቱም አሰልጣኙን ተከትሎ በስራ ላይ የሌሉ ባለሙያዎች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...