መነሻ ገጽ አፍሪካ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዝግጅቱን በአዳማ ከተማ አጠናክሮ መስራቱን ቀጥሏል !!
አፍሪካዋልያዎቹዜናዎች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዝግጅቱን በአዳማ ከተማ አጠናክሮ መስራቱን ቀጥሏል !!

አጋራ
አጋራ

ለአለም ዋንጫ ማጣሪያ ከጋና እና ዚምባቡዌ ብሔራዊ ቡድኖች ጋር በተከታታይ ላሉበት ጨዋታዎች ለ28 ተጫዋቾች ጥሪ በማቅረብ ዝግጅቱን የጀመረዉ የአሰልጣኝ ዉበቱ አባተ ስብስብ ከነሀሴ 04/12/2013 ዓ.ም ጀምሮ ዝግጅቱን በመከወን ላይ ይገኛል።

በአሠልጣኝ ዉበቱ አባተ ጥሪ ከተደረገላቸው 28ተጫዋቾች መካከል በቋሚነት ዝግጅት ወደ ሚያደርጉበት አዳማ ከተማ ያመሩት 24ተጫዋቾች ብቻ እንደሆኑ ታዉቋል። የፈረሰኞቹ አማካይ ሀይደር ሸረፋ እና በቅርቡ ወደ አልጀሪያዉ ክለብ ዝዉዉር ለማድረግ ሂደት ላይ የሚገኘዉ የቀድሞዉ የአፄዎቹ አጥቂ ሙጂብ ቃሲም በቋሚነት ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር ተቀላቅለዉ ዝግጅት መጀመር ያልቻሉ ሲሆን በአንፃሩ አጥቂዉ አቡበከር ናስር እና የጣና ሞገዶቹ አማካይ ፍፁም ዓለሙ ፍቃድ በመጠየቃቸው ምክንያት እስከ አሁን ድረስ ብሔራዊ ቡድኑን መቀላቀል ባይችሉም በቅርቡ ወደ አዳማ አምርተው ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር ዝግጅታቸውን እንደሚጀምሩ ይጠበቃል።

 

በተያያዘም አሰልጣኝ ዉበቱ ለሁለት አዳዲስ ተጫዋቾች ጥሪ ማድረጋቸውም ይታወሳል። በዚህም መሰረት አጥቂዉ ቸርነት ጉግሳ እና አማካዩ በዛብህ መለዮ ወደ አዳማ በመጓዝ ስብስቡን መቀላቀላቸውን ታዉቋል።

ማረፊያቸውን በኤክስኪዩቲቭ ሆቴል ያደረጉት ዋልያዎቹ ልምምዳቸውን በቀን ሁለት ጊዜ በማከናወን ላይም ይገኛሉ። ብሔራዊ ቡድኑ በወርሃ ነሐሴ መጨረሻ እና ጳጉሜ ወስጥ ከሚያከናውናቸው የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች በፊት የወዳጅነት ጨዋታ በቅርቡ እንደሚያደርግም ሀትሪክ ያገኘችው መረጃ ያመላክታል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...