የፊታችን ማክሰኞ ይፋ በሚደረገው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ድልድል አስቀድሞ የሀገራት ቋት መታወቁ ተገልጿል።
ሀገራችን ኢትዮጵያም በመጨረሻው ቋት አራት ላይ የተቀመጠች ሲሆን በምድብ ድልዱሉ ከእያንዳንዱ ቋት የተመረጡ አንድ አንድ ሀገራት የሚደርሷት ይሆናል።
በዚህም መሰረት :-
#ቋት_አንድ :- ካሜሮን ፣ አልጄርያ ፣ ሴኔጋል ፣ ቱኒዚያ ፣ ሞሮኮ እና ናይጄርያ
#ቋት_ሁለት :- ግብፅ ፣ ጋና ፣ ኳትዲቯር ፣ ማሊ ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ጊኒ
#ቋት_ሶስት :- ኬፕ ቨርዴ ፣ ጋቦን ፣ ሞሪታንያ ፣ ሴራሊዮን ፣ ዚምቧቡዌ እና ጊኒ ቢሳው
#ቋት_አራት :- ማላዊ ፣ ሱዳን ፣ ኢኳቶሪያል ጊኒ ፣ ኮሞሮስ ፣ ኢትዮጵያ ፣ ጋምቢያ ሆነው ተደልድለዋል ።
ሀገራት በፊፋ የአለም ሀገራት ደረጃቸው መሰረት በአራቱ ቋት ስር ሊደለደሉ ችለዋል። አንድ ሀገር በተደለደለበት ቋት ስር ካለ ሀገር ጋር አይገናኝም ወይም አብሮ በአንድ ምድብ አይደለደልም ።
አስተያየት ይስጡ