መነሻ ገጽ አፍሪካ ዋንጫ የዋልያዎቹ ሁለት ወሳኝ ተጫዋቾች ጉዳት ላይ ይገኛሉ
አፍሪካ ዋንጫአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

የዋልያዎቹ ሁለት ወሳኝ ተጫዋቾች ጉዳት ላይ ይገኛሉ

አጋራ
አጋራ

በ2023 ለሚደረገዉ የኮትዲቫር የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታቸዉን እያደረጉ የሚገኙት ዋልያዎቹ ከዕሁዱ የማላዊ ሽንፈት በኋላ በትላንትናው ዕለት ልምምዳቸውን አከናውነዋል።

በምድባቸዉን ሁለተኛ ጨዋታ የፊታችን ሀሙስ ምሽት 1ሰዓት ላይ በማላዊ ቤንጉ ስታዲየም ከግብፅ ብሐራዊ ቡድን ጋር የሚያደርጉት ዋልያዎቹ በጉዳት ምክንያት የሁለት ወሳኝ ተጫዋቾቻቸውን ግልጋሎት የማግኘታቸው ነገር አጠራጣሪ ሆኖአል።

የተከላካዩ መስመር ተጫዋቹ ያሬድ ባየ እና አማካዩ ሱራፌል ዳኛቸዉ ከዕሁዱ የማላዊ ጨዋታ በኋላ መጠነኛ ጉዳት በማስተናገዳቸዉ ምክንያት በትላንትናው ዕለት ብሐራዊ ቡድኑ በነበረዉ ልምምድ ላይ ቢገኙም ሙሉ ለሙሉ ልምምድ መስራት አለመቻላቸውን አሰልጣኝ ዉበቱ አባተ ገልጸዋል።

አሰልጣኙ አያይዘውም የሁለቱን ተጫዋቾች ጉዳት በተመለከተ በቀጣይ ቀናት በሚኖሩ ልምምዶች ላይ እንደሚገመገምም ተናግረዋል። ዋልያዎቹ የፊታችን ሀሙስ ምሽት 1ሰዓት ላይ ከፈርኦኖቹ ጋር የምድብ ሁለተኛ ጨዋታቸውን የሚያደርጉም ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...