መነሻ ገጽ ሰበታ ከተማ የሰበታ ከተማ ክለብ እና የተጫዋቾቹ ውዝግብ አሁንም ቀጥሏል
ሰበታ ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሰበታ ከተማ ክለብ እና የተጫዋቾቹ ውዝግብ አሁንም ቀጥሏል

አጋራ
አጋራ

በ2014 ዓ.ም በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ላይ በመሳተፍ ላይ የሚገኘው የሰበታ ከተማ እግር ኳስ ክለብ በውድድር ዓመቱ በተደጋጋሚ የደመወዝ እና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄዎችን በጊዜው መክፈል ባለመቻሉ ምክነያት ከተጫዋቾቹ በተደጋጋሚ ቅሬታ ሲቀርብበት እኛም መዘገባችን ይታወሳል ።

ተጫዋቾቹ ለሚመለከታቸው አካላት ቅሬታዎቻቸውን ካቀረቡ በኋላ በሚደረጉ ንግግሮች ወደ ውድድር ተመልሰው የክለቡን ማልያ ለብሰው በመጫወት ላይ ቢገኙም ያቀረቡት ጥያቄ በተገቢው መልኩ ሳይፈታ በመቅረቱ በዛሬው ዕለት ሌላ የቅሬታ ደብዳቤ ለሚመለከታቸው አካላት ለማስገባት ተገደዋል ።

የቅሬታ ደብዳቤው ላይ የክለቡ 21 ተጫዋቾች ስም እና ፊርማ ያረፈበት ሲሆን በዛው ላይ እንደተገለጸውም ከሆነ የደመወዝ እና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ አቅርበው መልስ ሳያገኙ በቀሩበት ጊዜ ክለቡ በ25/09/14 ዓ.ም ለፌዴሬሽኑ በስራ ገበታቸው ላይ አልተገኙም ብሎ በደብዳቤ እንዳመለከተባቸው ገልፀዋል ።

ነገር ግን ክለቡ ለተጫዋቾቹ መክፈል የሚገባውን የ2013 ዓ.ም ከሁለት እስከ አራት ወራት ድረስ ክፍያ እንዳልከፈላቸው እና የ2014 ደግሞ የመጋቢት ፤ የሚያዝያ እና የግንቦት ወራት ክፍያ እንዳልተከፈላቸው በመግለፅ በቀጣዮቹ 3 ቀናት ውስጥ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል ።

ሰበታ ከተማ በሊጉ የ25 ሳምንታት ጉዞ 4 ድል ፤ 5 አቻ እና 13 ሽንፈት አስተናግዶ በደረጃ ሰንጠረዡ 16ኛ ላይ ይገኛል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...