ኢትዮጵያ መድን የአጋማሹን አራተኛውን ፈራሚ አግኝቷል።
በአሰልጣኝ ገብረመድኅን ሐይሌ የሚመሩት የወቅቱ የሊጉ ሻምፒዮን ኢትዮጵያ መድን ከቀናቶች በፊት ከመቐለ 70 እንደርታ በውሰት ተከላካዩን አማኑኤል ልዑልን ፣ ብሩንዲያዊውን የመስመር አጥቂ አልፍሬድ ኑኩሩንዚዛን እና አጥቂው ሳሙኤል ሳሊሶን በአጋማሹ የዝውውር መስኮት ማስፈረማቸው የሚታወስ ሲሆን አሁን ደግሞ ባለፈው የውድድር ዘመን በመቐለ 70 እንደርታን ተቀላቅሎ በተለይ ከቆሙ ኳሶች በግንባር በማስቆጠር የሚታወሰውን የተከላካይ አማካይ እና የተከላካይ ተጫዋቹን ቤንጃሚን ኮቴ ወደ ሀገራችን ተመልሶ ለኢትዮጵያ መድን ፊርማውን አኑሯል።
የ30 አመቱ ይህ ተጫዋች ለሀገሩ ጋና ካሬላ ዩናይትድ እና ህርትስ ኦፍ ኦክ እንዲሁም ለግብፁ ኢስተርን ካምፓኒ እና ለሳውዲ አረቢያው አል ታቃዶም ክለቦች ከተጫወተ በኋላ ወደ ሀገራችን ባለፈው አመት መጥቶ ለመቐለ የተጫወተ ሲሆን ከመቐለ ከተለያየ በኋላ ግን ክለብ አልባ ሆኖ እንደነበር መረጃው ያሳያል ይህም ተጫዋች ዛሬ በይፋ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ መድንን ተቀላቅሎ ወደ ሀዋሳ ማምራቱን አረጋግጠናል።
አስተያየት ይስጡ