ትላንት ቢኒያም ፍቅሩን የግሉ ያደረገው ሸገር ከተማ አንተነህ ተፈራን ለቋል።
ከአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ጋር በገባው ተደጋጋሚ ሰጣገባ በክለቡ ደስተኛ ካልነበሩ አራት ተጫዋቾች አንዱ የነበረው አጥቂው አንተነህ ተፈራ በመጨረሻም ክለቡን ለቆ ማረፊያው ባህርዳር ሆኗል። ከትውልድ ሀገሩ አዶላ ወዩ እና ሻኪሶ በኋላ በኢትዮጵያ ቡና የሦስት አመት ቆይታን በማድረግ ከብዙሃኑ ጋር መተዋወቅ የቻለ ሲሆን በመጨረሻም ሁለት አመት ፈርሞ ስድስት ወር ብቻ ከተጫወተበት ሸገር ከተማ ጋር ባስገባው መልቀቂያ በመጨረሻም ክለቡ ተቀብሎት ማረፊያው የጣና ሞገዱ እስከ አመቱ መጨረሻ ሆኗል።
ሸገር ከተማ በምትኩ ትላንት ቢኒያም ፍቅሩን ማስፈረሙ ይታወሳል።


