የዝውውር ዜና
ቡድኑን በቀጣይ አመት ተፎካካሪ ለማድረግ በማቀድ ከፍተኛ ዝውውር በማድረግ ላይ የሚገኙት የጊዮን ንግስቶቹ የሁለት ተጨማሪ ተጨዋቾች ውል አጠናቀዋል ። በዛሬ እለት ፍርማቸው ከሳረፉት መሀከል ከልደታ ክ/ከተማ አሪፍ ጊዜ ያሳለፈችው ትግስት ሀይሌ በአንድ ዓመት ውል መቀላቀል ችላለች በተጨማሪም ቤቴልሄም ከፍያለው መዳረሻዋን ባህርዳር ከተማ አድርጋለች ።
በሌላ የዝውውር ዜና ሸገር ከተማ ሁለት ተጨዋቾች ማስፈረም ችሏል በ አሰልጣኝ ደሪባ የሚመራው የከፍተኛ ሊግ አሸናፊዎቹ ሶፋኒት ተፈራ እና ቤቴሌም ታምሩ በአንድ ዓመት ውል ማስፈረም ችለዋል ።



