በዘንድሮው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባልተጠበቀ ጉዞ ላይ የሚገኘው ሀዋሳ ከተማ ከአሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉ ጋር ከተለያየ በኋላ በጊዜያዊ አሰልጣኝ ወንድማገኝ ተሾመ ሲመራ መቆየቱ ይታወቃል።
በጊዜያዊ አሰልጣኙ እየተመራም ከወራጅ ቀጠናው ለመላቀቅ የተቸገረው ሀዋሳ ከተማ አስቀድሞ በተጫዋችነት እና አሰልጣኝነት ክለቡን ያገለገለውን ሙሉጌታ ምህረትን በዋና አሰልጣኝነት መሾሙ ተረጋግጧል።
አሰልጣኝ ሙሉጌታ ቡድኑን እየመራ የመጀመሪያ ጨዋታውን በኢትዮጵያ ዋንጫ ከአራት ቀናት በኋላ በሀዋሳ ሰው ሰራሽ ሜዳ ላይ ከነገሌ አርሲ ጋር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።



