የተጠናቀቀዉን የውድድር አመት በአሰልጣኝ ገ/ክርስቶስ ቢራራ እየተመራ ሊጉን በሁለተኝነት ማጠናቀቅ የቻለዉ መቻል ከቀናት በፊት የአሰልጣኙን ዉል ካራዘመ በኋላ አሁን ደግሞ አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ስብስቡ መቀላቀሉን ቀጥሏል።
አንደኛዉ ያለፉትን አስር ያክል አመታት በኢትዮጵያ ቡና ቤት መጫወት የቻለዉ የአማካይ ስፍራ ተጫዋቹ አማኑኤል ዮሐንስ ሲሆን ፤ በተጨማሪም በኢትዮጵያ መድን የእግርኳስ ሂዎቱን አንድ ብሎ የጀመረዉ እና በወልቂጤ ከተማ እንዲሁም ያለፈዉን አመት ደግሞ በቡናማዎቹ ቤት ማሳለፍ የቻለዉ የአጥቂ አማካዩ አብዱልከሪም ወርቁ በሁለት አመት ዉል መቻልን መቀላቀላቸዉ ታውቋል።
እንደሚታወቀው መቻል በትላንትናው ዕለት ዳንኤል ደርቤን እና ፊሊሞን ገ/ፃዲቅን ወደ ስብስቡ መቀላቀሉ ይታወቃል።



