ፈረሰኞቹ ከ20 ዓመት በታች ተጨዋች የሆኑት የአጥቂ ስፍራ ተጫዋች ክብር አክሊሉ ፣ የቀኝ ተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ቴዎድሮስ አሰፋ ፣ የአማካኝ ስፍራ ተጫዋች የሆኑት ፋኑኤል አዳሙ እና ይትባረክ ሰጠኝ ለሶስት ዓመት የሚያቆያቸውን ፊርማ አኑረዋል፡፡
ፈረሰኞቹ ካደረጋቸው ሶስት ጨዋታዎች ሁለቱን በማሸነፍ እና በአንድ ሽንፈት በስድስት ነጥብ እና በአንድ የግብ ክፍያ በደረጃ ሰንጠረዡ ሰባተኛ ደረጃን ይዘዋል።
በሁለተኛ ሳምንት ከመድን ጋር የነበራቸው ጨዋታ በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ምክንያት መራዘሙ አይዘነጋም።



