ከፈረሰኞቹ ጋር አምስት የፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ ያነሱት ሰርቪያዊው አሰልጣኝ ወደ ቀድሞው ክለባቸው ተመልሰዋል።

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ ከታዩ ድንቅ የውጪ ዜጋ አሰልጣኞች መካከል አንዱ መሆን የቻሉት ሰርቪያዊው አሰልጣኝ ሰርዲ ሚሊት ሚቾ ወደ ቀድሞው ክለባቸው ቅዱስ ጊዮርጊስ በአማካሪነት መመለሳቸውን አውቀናል። አስራ ሁለት ክለቦችን እና አምስት ሀገራት ደግሞ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ መሰልጠን የቻሉት አሰልጣኙ እንደ ኦርላንዶ ፓይሬት ፣ ያንጋ አፍሪካ ፣ አልሂላል እና ዛማሌክ ያሉ የአፍሪካ ስመ ጥር ክለቦችን ማሰልጠን ቢችሉም እንደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን ስኬታማ የሆኑበት ቡድን የለም ከ1997 እስከ 2002 ክለቡን ያሰለጠኑት አሰልጣኙ በፈረሰኞቹ ቤት አምስት የፕሪምየር ሊግ ዋንጫዎችን ያነሱ ሲሆን አንድ የጥሎ ማለፍ ዋንጫን ከክለቡ ጋር ማንሳት ችለዋል።

ትላንት በአዲስ አበባ ስታዲየም የፕሪምየር ሊጉን ጨዋታዎች ሲመለከቱ የነበሩት እና በቅርቡ በአልጄሪያ ሊግ ከሚወዳደረ ኢ ኤስ ስቲፍ ጋር በመለያየት ለዕረፍት ትዳር ወዳገኙባችፈት ኢትዮጵያ የመጡት አሰልጣኝ ሚቾ እስከ ውድድር ዘመኑ ፍፃሜ ድረስ አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝን በሜዳ እና ከሜዳ ውጪ በጨዋታ እና ከጨዋታ ውጪ የቀድሞው ክለባቸውን እያገዙ አመቱን እንደሚቆዩ የሰማን ሲሆን እንዳገሁት መረጃ ከሆነ ግን ከሌሎች የአፍሪካ ክለቦች ጋር ንግግር ላይ የሚገኙት አሰልጣኙ የቅዱስ ጊዮርጊስን የፋይናንስ ስርዓት መሻሻልን ተከትሎ ጥሩ ክፍያን የሚያገኙ ከሆነ ቀጣዩን አመት በክለቡ የዋና አሰልጣኝነት ሚና ልናያቸው እንደምንችልም ማወቅ ችያለሁ።
አስተያየት ይስጡ