የዚህ ሳምንት የሀትሪክ ስፖርት ተረኛ እንግዳችን አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ይሆናል ።
ሀትሪክ : እግር ኳስ እንዴት ማሰልጠን ጀመርክ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰለጠንከው ቡድንስ ምን ነበር ?
ስዩም : ማሰልጠን የጀመርኩት በተለያዩ ጊዚያት የወሎና የኢሉባቦር ስፖርት ኮሚሽን የቴክኒክ ኃላፊ ሆኜ ምርጥ ቡድኖቹን በማሰልጠን ሲሆን የጀመርኩት ከዚህ ኃላፊነት በኋላ በ1983 ዓ.ም የቅ/ጊዮርጊስን ወጣት ቡድን በማሰልጠን ነዉ የጀመርኩት !
- ማሰታውቂያ -

ሀትሪክ : በእግር ኳስ ሂወትህ የት የት መጫወት ቻልክ ?
ስዩም : መጫወት የጀመርኩት የደሴ ጤና ጥበቃ ቡድንና የወሎ ምርጥን በመወከል ነዉ ።
ሀትሪክ : እግር ኳስ እንዴት በምን አጋጣሚ አቆምክ !
ስዩም : ያቆምኩት ለኢትዮጵያ ወጣት ቡድን ተመርጨ ልምምድ ላይ ባጋጠመኝ የጡንቻ መሰንጠቅ ነዉ ።
ሀትሪክ : ከ ሰላሳ ዓመት በዋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ያለፈውን ናሽናል ቲም እንዴት ትገልፀዋለው
ስዩም : ከ31 ዓመት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ያለፈዉ ቡድናችን መላ ሀገሪቱን በአንድነት ያስተሳሰረ ብቻ ሳይሆን በዉጭ ሀገር የሚኖሩትን ዲያስፖራ ወንድምና እህቶቻችንን በልዩ ስሜት እንባ ያራጨ ታሪካዊ ቡድን ነበር ።
ሀትሪክ : እስኪ ኮች በአሰልጣኝነት ሂወት ትልቁን የሀገራችን ዋንጫ ማሳካት ችለዋል ስሜቱን ገለፅ
ስዩም : የሀገሪቱን ታላቅ ዋንጫ ከቅ/ጊዮርጊስ እንዲሁም ከፋሲል ከነማ ጋር ሁኜ አሳክቻለሁ ስሜቱን መግለፅ እንዲህ በዋዛ የሚቻል አይደለም ..ለነዚህ ስኬቶች ብዙ ዉጣ ዉረዶችን አልፌበታለሁና !!
ሀትሪክ : በ አሰልጣኝነት ዘመነህ የሚደንቅህ ተጨዋች ማን ነው ??
ስዩም : የማደንቀዉ ተጨዋች በቅርብ ከዚህ ዓለም ድካም ያረፈዉን “ሙሉጌታ ከበደን” ነዉ ።
ሀትሪክ : እስኪ የፋሲል ከነማ ቆይታ እና ስለደጋፊው ምን ትላለህ
ስዩም : ፋሲል ከነማ እጅግ የገዘፈ ደጋፊ ያለዉ በቆየሁባቸዉ ዓመታት ደጋፊዎች ከጎናችን ሁነዉ ብርታትና ጥንካሬ የሆኑን ለመጀመሪያ ጊዜ DSTV ስርጭት በጀመረበት ሊጋችን ታሪካዊዉን ዋንጫ ያገኜሁበት በመሆኑ በስፖርቱ ቆይታዬ የስኬቴ ልዩ ትዉስታ አድርጌ እወስደዋለሁ ።
ሀትሪክ : በተቃራኒ ከገጠምካቸው በጣም ብዙ አሰልጣኞች የከበደ ወይም የፈተነህ አሰልጣኝ ማን ነው ?
ስዩም : እከሌ ማለት ባልችልም ሁሉም ተጋጣሚዎቻችን በጊዮርጊስም ሆነ በፋሲል ቆይታዬ ፈተናዉን የተወጣንበት መንገድ አስቸጋሪነቱ የተበራከተ ነበርና ለዚህም ሁሉም አሰልጣኞች የራሳቸዉ
ዝግጅት ጥንካሬ ነበር
ሀትሪክ : የ አሰልጣኝ ስዩም የምንግዜም ምርጥ ተጨዋች ማነው አንድ ብቻ ነው መጥቀስ ሚቻለው ።
ስዩም : ዘመን ከነበሩት ሙሉጌታ ከበደን/ነፍስ ይማር/
ሀትሪክ : በቀጣይ ዓመት ፕሪሚየር ሊጉ በ 20 ቡድኖች ይደረጋል ኮች እንደ አሰልጣኝ ምን አስተያየት ትሰጣለህ ?
ስዩም : ከቁጥሩ መጨመር ጋር ተያይዞ ፎርማቱ ካልተቀየረ አሁን እንደሚደረገዉ አንድ ከተማ ላይ መሆን በልምምድ ሜዳም ሆነ በተጓዳኝ ነገሮች ችግሩ ይበልጥ ይገዝፋል
ሀትሪክ : የዘንድሮ የውድድር አመት ግለፅ ብትባል እንደተመልካች ?
ስዩም : ብዙ የተወላገዱ ነገሮች የበዛበት ዓመት ነበር ለዚህም ነዉ ወራጅ ቡድን እንኳን የተረፈዉ ።
ሀትሪክ : የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከ ላይሰንስ ጋር ያወጣው ህግ አግባባብ ነው ?? ደንገት መሆኑስ ክለቦች ላይ ሚያመጣው ተፅኖስ ??
ስዩም : ድንገት መሆኑ በርካታ አሰልጣኞችን ይጎዳል ሆኖም ይህ ዉሳኔ ዘንድሮ በነበረዉ የዉድድር አጋማሽ ወቅት ቀድሞ ቢገለፅ በዚህ ህግ የሚጎዱት የራሳቸዉን የሥነልቦና ዝግጅት ማድረግ ይቻላቸዉ ነበር ።
ሀትሪክ : አሁን ፈታኝ ጥያቄ :- ከ አዳነ ግርማ እና ሰላዲን ሰይድ?
:ከ ከሱራፌል ዳኛቸው እና በዛበህ መለዮ?
: ከ ያሬድ ባዬ እና አስቻለው ታመነ ??
ስዩም :
- ሰላዲን
- ሱራፌል
- አስቻለዉ
ሀትሪክ : በቀጣይ ምን ታሰበ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ተመለሳለህ ??
ስዩም : አዎ እመለሳለሁ!
ሀትሪክ : የአሰልጣኝ ስዩም የምንግዜም ምርጥ 11 ተጨዋች እነማን ናቸው ???
ስዩም :
- በ4:3:3 ፎርሜሽን
- በረኛ : ተካበ ዘዉዴ
- ተከላካይ
አማኑኤል እያሱ፣ በቀለ ብርሃኑ ፣ ዳኛቸዉ ደምሴ ፣ ዮሐንስ ሣህሌ - አማካዮች
ሰለሞን ቸርኬ ፣ ተ/ሚካኤል ዳኜ ፣ ማትያስ ሀ/ማርያም - አጥቂዎች
ሙሉጌታ ወ/የስ ፣ ሙሉጌታ ከበደ እና ገ/መድህን ኃይሌ ናቸው ።
ሀትሪክ ስፖርትም ከ አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ጋር ያደረግነውን ቆይታ በዚህ የቋጨን ሲሆን በሚቀጥለው ሳምንት ከሌላ እንግዳ ጋር እስክንገናኝ መልካም ሳምንት ።


