መነሻ ገጽ ሲዳማ ቡና ሲዳማ ቡና ሁለት የመስመር አጥቂ ተጫዋቾችን አስፈርሟል።
ሲዳማ ቡናዜናዎችየዝውውር ዜናዎች

ሲዳማ ቡና ሁለት የመስመር አጥቂ ተጫዋቾችን አስፈርሟል።

አጋራ
አጋራ

በዉድድር አመቱ በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ ባልተጠበቀ መልኩ በወራጅ ቀጠናዉ ላይ ለወራት ያክል ላለመዉረድ ሲፎካከር የነበረዉ ሲዳማ ቡና በዉድድሩ አመቱ አጋማሽ ላይ የቀድሞዉን አሰልጣኙን ዘርዓይ ሙሉ በማሰናበት መቀሌ 70 እንደርታ በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ አለመሳተፉን ተከትሎ ያለ ክለብ የቆዩትን አሰልጣኝ ገ/መድህን ሀይሌን በዋና አሰልጣኝነት በመቅጠር በሊጉ ለመቆየት ችሏል።

አሁን ደግሞ ይበልጥ ራሱን ለማጠናከር በዝዉዉር መስኩቱ ላይ በንቃት እየተሳተፉ የሚገኙት ሲዳማ ቡናዎች የከፍተኛ ሊግ ምድብ ለ ተሳታፊ ከሆነዉ ኮልፌ ቀራኒዮ የመስመር አጥቂ ተጫዋቾቹን ብሩክ ሙሉጌታ እና አንዋር ዱላ በዛሬዉ ዕለት ማስፈረማቸዉን ይፋ አድርገዋል።

የትግራይ ክልል ክለቦች በቀጣይ አመት በሊጉ የማይሳተፉ ከሆነ እነርሱን ለመተካት በሚል በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም በተዘጋጀው ዉድድር ላይ ጥሩ ብቃትን ማሳየት የቻሉት ሁለቱ ተጫዋቾች ምንም እንኳን ክለባቸዉ ኮልፌ ቀራኒዮ በቀጣይ አመት በሊጉ የሚያሳትፈውን ደረጃ መያዝ ባይቻልም በአዲሱ የዉድድር አመት ተጫዋቾቹን በአዲስ ክለብ የምንመለከታቸዉ ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...