ዩጋንዳዊው የሲዳማ ቡና የግብ ዘብ ከማንኛውም እግር ኳስ ታግዷል።
በዩጋንዳ ፕሪምየር ሊግ ባለፈው የውድድር ዘመን ኤክስፕረስ ለተባለ የሀገሩ ክለብ ሲጫወት ቡድኑ በኪታራ ቡድን መስከረም ወር ላይ 7ለ0 ሲሸነፍ ይህ ዘንድሮ ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ መጥቶ ለሲዳማ ቡና በመጫወት ላይ የሚገኘው የግብ ዘቡ ኢማኑኤል ካልም እና ሦስት የቡድን ጓደኞቹ አሰልጣኙን ጨምሮ ሆን ብለው ከአቋማሪ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት በመፍጠር ውጤቱ እንዲቀየር በማድረጉ በወቅቱ ጥርጣሬ ውስጥ ገብቶ መረጃ ሲሰበስብ የነበረው የሀገሪቱ የእግር ኳስ ፌድሬሽን ላለፉት 11 ወራት ከፊፋ ጋር በቅንጅት ምርመራን ሲያደርግ መረጃን በማግኘቱ የተነሳ ኢማኑኤል ካልም እና ጎደኞች በሚሊዮን የሚቆጠር የዩጋንዳ ሽልንግትን ለጨዋታ ማጭበርበር እንዲረዳው በመቀበሉ መረጃም በመገኘቱ ከማንኛውም እግር ኳስ ዕገዳ ተወስኖበታል ሲል ከሀገሪቱ ፌድሬሽን ያገኘሁት መረጃ ይጠቁማል።
ከዚህ በፊትም ለቅዱስ ጊዮርጊስ የተጫወተው ኬኒያዊው ግብ ጠባቂ ፓትሪክ ማታሲ በተመሳሳይ ማጭበርበር መከሰሱ ይታወሳል።
አስተያየት ይስጡ