በሴካፋ ለነገሱት ሁለት ወጣቶች ተስማሚ የሆነ የጨዋታ አቀራረብን ፈልጌ ነው አሰልጣኝ ካሳዬን የፈለኩት ብሏል ክለቡ።
በኢትዮጵያ እግር ኳስ ላይ በተለየ የጨዋታ መንገድ የሚታወቀው አሰልጣኝ ካሳዬ አራጌ ከአስራ ሰባታት አመታት በኋላ ተመልሶ በተጫዋችት እና በአሰልጣኝነት ያለፈበትን ኢትዮጵያ ቡናን 2012 የውድድር ዘመን በመረከብ እስከ 2014 የውድድር ዘመን ከቆየ በኋላ በተለይ ከክለቡ ስራ አስኪያጅ በነበራቸው ሰጣ ገባ በመጨረሻም መሰናበታቸው ይታወሳል።
ከስልጠናው አለም ያለፉትን አራት አመታት በመራቅ በሀገረ አሜሪካ ቆይታን ያደረጉትን እና በመሐል የፋስት ትራክ ቢ ላይሰንስን ለመውሰድ እንዲሁም ከፋሲል ከነማ ጋር ለመነጋገር መመለሳቸው የሚታወስ ሲሆን አሁን ግን አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለን በማሰናበት ከደቂቃዎች በፊት በረዳት አሰልጣኙ እያሱ መርሀፅድቅ ልምምድ የሰራው ሸገር ከተማ አሰልጣኙን ለመሾም የክለቡ አመራሮች ከአሰልጣኙ ጋር በስልክ ያወሩ ሲሆን አሰልጣኙን ወደ ሀገር ውስጥ በመምጣት ለክለቡ የሁለት አመት ፊርማውን ያኖራል ተብሎ ይጠበቃል።
እንዳገኘሁት ዝርዝር መረጃ ከሆነ በቅርቡ ከኢትዮጵያ ከሀያ አመት በታች ብሔራዊ ቡድን የፈረሙት ቢኒያም አብረሃ እና ዳዊት ካሳውን ያማከለ የጨዋታ መንገድን ክለቡ መምረጡ አሰልጣኙን ፈላጊ እንዳደረጋቸው ማረጋገጥ ችያለሁ።


