ረዳት አሰልጣኙን ዋና አሰልጣኝ ያደረገው ሸገር ከተማ ከአንድ ተጫዋች ጋር በመለያየት በሞትኩ አዲስ ተጫዋች ተክቷል።
ረዳት አሰልጣኙ ዶ/ር እያሱ መርሀፅድቅን ዋና አሰልጣኝ ያደረገው ሸገር ከተማ ከአንተነህ ተፈራ ጋር በመለያየት በምትኩ ቢኒያም ፍቅሬን ያስፈረሙ ሲሆን አሁን ደግሞ ከቀድሞው የጅማ አባጅፋር ፣ አዳማ ከተማ ተጫዋች የነበረው ሁለገቡ ተጫዋች አድናን ረሻድ ጋር ቀሪ የአንድ አመት ከስድስት ወራት ውል እየቀረው በመለያየት በምትኩ የቀድሞው የአዳማ ከተማ እና ሀዋሳ ከተማ የመስመር አጥቂው ዮሴፍ ታረቀኝ ባስገባው የልቀቁኝ ጥያቄ ቀሪ የስድስት ወራት ውል ከቀረው መቻል ጋር በመለያየት ማረፊያው ሸገር ከተማ ሆኗል።
ከሸገር ከተማ ጋር የተለያየው አድናን ከተለያዩ የፕሪምየር ሊግ ክለቦች ጋር እየተነገረ ሲሆን ማረፊያውም በቅርቡ ይታወቃል ተብሎ ይጠበቃል።



