ተሰናባቹ አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ሸገር ከተማን ቴክኒክ ሀላፊ ሆነው ይመሩታል።
በቅርቡ ከሸገር ከተማ አሰልጣኝነት ተነስተው በምትኩ በረዳት አሰልጣኙ ዶ/ር እያሱ መርሀፅድቅ የተተኩት አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ በክለቡ ቢሰናበቱም ክለቡ ለአሰልጣኙ ከፍተኛ ክፍያን የመክፈል ግዴታ ውስጥ ስለሚገባ ከሰሞኑ በልምምድ ሜዳዎች ላይ እየተገኙ ክለቡን በቴክኒካል ጉዳዮች እንዲያማክሩ የተደረጉ ሲሆን ውላቸው እስኪጠናቀቅም ክለቡን በቴክኒክ ጉዳዮች እንዲያማክሩ በመመረጣቸው ዛሬ ሀዋሳ ላይ ከክለቡ ጋር ተገናኝተዋል።
አሰልጣኙም በአሁኑ ሰዓት ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ሜዳ ላይ የአርባምንጭ ከተማ እና ነገሌ አርሲን ጨዋታ የታደሙ ሲሆን ማምሻውን ሸገር ከተማ ከ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሚኖራቸው ጨዋታ ስራቸውን ትሪቡን ሆነው በቴክኒክ ያገለግላሉ።



