ከአሰልጣኝ ውበቱ አባተ ጋር የተለያዩት ሰበታ ከተማዎች የተጫዋቾቻቸውን ውል እያራዘሙ ይገኛሉ ።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ድንቅ ብቃቱን ሲያሳይ የቆየው አንተነህ ተስፋዬ በሰበታ ቤት ለተጨማሪ ዓመታት ለመቆየት መስማማቱ ተገልጿል ።
ከ አንተነህ ተስፋዬ በተጨማሪ ሀይለሚካኤል አደፍርስ ሌላኛው በሰበታ ከተማ ቤት ለመቆየት የተስማማ ተጫዋች ነው ።ሰበታ ከተማዎች ከውበቱ አባተ ጋር ከተለያዩ በኋላ ስማቸው ከተለያዩ አሰልጣኝ ጋር እየተያያዘ ሲገኝ ይፋዊ ቅጥር እስከ አሁን አላካሄዱም ።