መነሻ ገጽ ሀዲያ ሆሳዕና ሀድያ ሆሳዕና ወሳኝ ተጨዋቾቹን ሊያጣ ነው
ሀዲያ ሆሳዕናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ሀድያ ሆሳዕና ወሳኝ ተጨዋቾቹን ሊያጣ ነው

አጋራ
አጋራ


ሀዲያ ሆሳዕና ያስፈረማቸውን ተጨዋቾች የማጣት ስጋት ውስጥ መግባቱ እየተነገረ ነው፡፡

የአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ጥቅማ ጥቅሞችና ቃል የገባውን ክፍያ በመፈፀም ለ1 አመት ማቆየቱን ያረጋገጠው ሀዲያ ሆሳዕና ለፋሲል ከነማ እንደፈረመው በረከት ደስታና ኢትዮጰያ ቡና እንዳቀናው አበበ ጥላሁን ቀሪ ተጨዋቾቹን የማጣት ስጋት ውስጥ መግባቱን የክለቡ ታማኝ ምንጮች በተለይ ለሀትሪክ ገልፀዋል፡፡

መረጃዎች እንደሚሉት አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለን ተከትለው ወደ ሆሳዕና ባቀኑት ተጨዋቾች መሀል ዳዋ ሆቴሳና ምኞት ደበበ ቃል የተገባልንን ክፍያ አልተፈፀመልንም በሚል ክለቡን ለመልቀቅና ወደ ሌላ ክለብ ለመጓዝ ማቀዳቸው እየተነገረ ነው ሁለቱም ተጨዋቾች “ክለቡ ቃል የገባልንን ሊፈፅምልን ካልቻለ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ሄደን አንፈርምም ወደ ሌላ ክለብ ለመሄድ እንገደዳለን” ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ ከአዳማ ወደ ሀዲያ ሆሳዕና ያቀኑት ተጨዋቾች ክፍያ ባለመፀሙና የተገባላቸው ቃል ባለመከበሩ ቅሬታ ውስጥም መግባታቸው ለሀትሪክ የደረሰው መረጃ ያስረዳል፡፡ በዚህ ቅሬታ ጉዳይ ምላሻቸውን የሰጡት የክለቡ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መላኩ ማዶሮ በበኩላቸው “ሀዲያ ሆሳዕና የተቻለውን እያደረገ ነው የትኛውም ክለብ ያላደረገውን ግማሽ ክፍያ በካሽ ሰጥተናቸዋል፤ ካሉን ተጨዋቾች ቅድሚያ ለነርሱ ሰጥተናል በቀጣይ ወር ሙሉውን እንጨርሳለን ይህንንም ነግረናቸዋል፤ ከዚህ በላይ ምን ይጠበቅብናል?” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ አቶ መላኩ እንደሚሉት “የክለቦች ፋይናንስ የሚመጣው ከመንግሥት ነው ዞኑ ያቀረበው የክልል ጥያቄ ተመልሶለት ሙሉ ሃሣቡ በዚህ አደረጃጀት ላይ በመሆኑ ባለው ነገር እያመቻቸን እነሱን ለማስደሰት እየጣርን ነው ሙሉ በሙሉ የአመቱን ክፈሉ ሲሉን ግን ይከብዳል?” ጠብቁን ይስተካከላል እያልናቸው ነው፡፡የሌሎቹም ተጨዋቾች ተሰርቶላቸዋል ከሁሉም በላይ ግን እንደኛ በካሽ የሰጠ የለም በቼክ ብቻ ነው ይህን ማወቅ አለባቸው” በማለት የክለቡን አቋም ለሀትሪክ ገልፀዋል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...