መነሻ ገጽ ሰበታ ከተማ ሰበታ ከተማ ከአጥቂዉ ጋር በስምምነት ተለያይቷል
ሰበታ ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

ሰበታ ከተማ ከአጥቂዉ ጋር በስምምነት ተለያይቷል

አጋራ
አጋራ

በክረምቱ የተጫዋቾች የዝዉዉር መስኮት ሰበታ ከተማን ተቀላቅሎ የነበረዉ ናሚቢያዊዉ አጥቂ ጁንያስ ናንጄቦ ከክለቡ ጋር በስምምነት መለያየቱ ተሰምቷል።

ከዚህ ቀደም ለወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ እና ድሬዳዋ ከተማ መጫዎት የቻለዉ አጥቂዉ ለሰበታ ከተማ ለመጫወት ፊርማዉን ካኖረ ከአራት ወራት ቆይታ በኋላ ከክለቡ ጋር በስምምነት መለያየቱ ዕርግጥ ሆኖአል።

ለመለያየታቸዉ እንደምክንያት የተጠቀሰዉም ተጫዋቹ ክለቡን ከተቀላቀለበት ጊዜ አንስቶ እስከ ሰባተኛዉ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በነበሩት ጨዋታዎች ላይ የነበረዉ ዕንቅስቃሴ እንደታሰበዉ መሆን አለመቻሉን የገለፁት የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ አለማየሁ ምንም እንኳን እኛ በአቋሙ ደስተኞች ባንሆንም ተጫዋቹ በራሱ ፍቃድ መልቀቂያ በማስገባቱ ምክንያት በስምምነት ለመለያየት መወሰናቸዉን ለሀትሪክ ስፖርት ድህረ-ገጽ ገልፀዋል ።

ተጫዋቹ በዛሬው ዕለትም ከሀዋሳ ወደ አዲስአበባ በማምራት ከክለቡ ሀላፊዎች ጋር በመገናኘት በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን ፅህፈት ቤት በመገኘት በስምምነት ዉላቸዉን እንደሚያፈርሱ ታዉቋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...